
__
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ቴህራን በአሜሪካ ለቀረበው የድርድር ዕቅድ የሰጠችው ምላሽ “ምክንያታዊ እና ለጋስ” እንደሆነ በመግለጽ፤ አሜሪካን ግን “ለአንድ ወገን ያደላ እና ምክንያታዊ ያልሆነ” አቋም ላይ ጸንታለች የሚል ክስ አቀረቡ።

ቅዳሜ 9 ሜይ 2026 ጥዋት 4:53:06
የትግራይ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክስርስቲያን ሲኖዶስ ባደረገው ጉባኤ፤ የጥንታዊቷ አክሱም መጠሪያ “ቅድስት አክሱም ጽዮን ከተማ” እንዲሆን መወሰኑን አስታወቀ። ቤተ ክርስቲያኗ፤ ይህንን ውሳኔ ተከትሎ በከተማዋ እንደ “መጠጥ እና ጫት” ሽያጭ ያሉ ተግባራት ላይ ክልከላ እንዲጣል እንደምትፈልግ እንዲሁም “የቅድስና ምልክት እንድታሳይ የሚያደርጉ ሕጎችን” እያወጣች መሆኑን ገልጻለች።

ዓርብ 27 ማርች 2026 ጥዋት 3:57:49
ገዢው ብልጽግና ፓርቲ ዕጩ ባላቀረበባቸው ከ80 በላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫዎች ውስጥ የተቃዋሚዎቹ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) እና የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) አመራሮች የሚወዳደሩባቸው የምርጫ ክልሎች እንደሚገኙ ቢቢሲ ተገንዝቧል።

ሐሙስ 2 ኤፕሪል 2026 ከሰዓት 5:42:05
የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በመራጮች የምዝገባ ሂደት ወቅት “ቤት ለቤት በመሄድ” ካርድ ውሰዱ ከሚል አንስቶ “ማኅበራዊ አገልግሎት ማግኘት” እንዲሁም “ከደሞዝ መቁረጥ ጋር በማያያዝ” በዜጎች ላይ ተጽዕኖ እስከማድረስ ያሉተግባራትን ማስተዋሉን ገለጸ።

ዓርብ 27 ማርች 2026 ጥዋት 11:29:08
ብልጽግና ፓርቲ፤ ምርጫ የመካሄዱ ነገር አጠራጣሪ በሆነበት ትግራይ ክልል ለሚገኙ የፓርላማ እና የክልል ምክር ቤት መቀመጫዎች አንድም ዕጩ አለማቅረቡን ቢቢቢ የተመለከተው የዕጩዎች ዝርዝር ያሳያል። ስድስት ተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች እና ሁለት ቅንጅቶች በበኩላቸው 101 ዕጩዎችን አስመዝግበዋል።

ረቡዕ 25 ማርች 2026 ከሰዓት 12:34:07
ብልጽግና ፓርቲ ግንቦት ላይ ይካሄዳል ተብሎ በሚጠበቀው ሰባተኛው አጠቃላይ ምርጫ ለአዲስ አበባ ከተማ ካቀረባቸው 154 ዕጩዎች ውስጥ 96 ያህሉ በባለፈው ምርጫ በመዲናዋ ያልተወዳደሩ እንደሆኑ ቢቢሲ ያደረገው ዳሰሳ ያሳያል። በመጪው ምርጫ በአዲስ አበባ ዕጩ ሆነው ካልቀረቡት ተመራጮች መካከል ምክትል ከንቲባው ጃንጥራር አባይ ይገኙበታል።

ማክሰኞ 24 ፌብሩዋሪ 2026 ጥዋት 9:48:54
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአማራ እና ትግራይ ክልሎች መካካል “አከራካሪ ሆነው የቆዩ” የተባሉትን አምስት የምርጫ ክልሎች በተመለከተ ከፌዴሬሽን ምክር ቤት ደርሶኛል ያለውን ውሳኔ ይፋ ካደረገ በኋላ የሁለቱ ክልሎች የፖለቲካ ተዋንያን በየፊናቸው መግለጫዎችን አውጥተዋል። በትግራይ በኩል ጊዜያዊ አስተዳደሩን ጨምሮ ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች ተቃውሟቸውን ሲያሰሙ፤ በአማራ በኩል የሚገኙት ደግሞ ለውሳኔው ድጋፋቸውን ገልጸዋል።

ሰኞ 27 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 3:52:40
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከሰባት ወር በኋላ በአገሪቱ ይካሄዳል ላለው ምርጫ ረቂቅ የጊዜ ሰሌዳ አዘጋጅቷል። በበርካታ የአገሪቱ ክፍሎች ውስጥ ያሉትን ግጭቶች እና አለመረጋጋት በመጥቀስ ተቃዋሚ ፖለቲከኞች ከምርጫው በፊት ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገቡ ጉዳዮች አሉ እያሉ ነው። በቀጣዮቹ ወራት ግጭቶችን በማስቆም ለምርጫ አመቺ ሁኔታን መፍጠር ይቻላል ወይ በሚለው ላይም እርግጠኞች አይደሉም። ምን አማራጭ አለ?

ዓርብ 14 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 4:09:31
አስር ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ስብስብ በዚህ ዓመት የሚካሄደው ምርጫ ነፃ፣ ፍትሃዊና ተዓማኒ እንዲሆን እና “ከአጃቢነት ያለፈ ተሳትፎ” እንዲኖራቸው የሚጠይቅ ቅድመ ሁኔታዎችን አቀረቡ። ራሳቸውን የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች አንድነት መድረክ (መድረክ) ሲሉ የሚጠሩት 10 የተቃዋሚ ፓርቲዎች ስብስብ ኅዳር 3/2018 ዓ.ም. በጋራ ባወጡት መግለጫ ላይ “ሕጋዊነትን ለመላበስ የሚደረጉ የፖለቲካ ትወናዎች” ሲሉ ከዚህ ቀደም የተደረጉ ምርጫዎችን በመኮነን፤ ምርጫዎቹ “ነፃ፣ ፍትሃዊ እና አሳታፊ፤ በውጤታቸውም ተዓማኒ እና በሕዝብ ተቀባይነት አላገኙም” ሲሉ ተችተዋል።

ሐሙስ 26 ፌብሩዋሪ 2026 ጥዋት 3:54:00
በአማራ ክልል ስላለው ወቅታዊ ሁኔታ እና ስለፓርቲው ማብራሪያ እንዲሰጡ ቢቢሲ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ከሆኑት ከአቶ ጋሻው መርሻ ጋር ቃለ ምልልስ አድርጓል። አቶ ጋሻው በአገራዊ፣ በክልላዊ እና በአብን ጉዳዮች ላይ የቀረቡላቸውን ጥያቄ ከሞላ ጎደል ከመለሱ በኋላ ቢቢሲን በወገንተኝነት በመክሰስ ቃለ ምልልሱን አቋርጠዋል። ቃለ ምልልሱን እንዲያቋርጡ ያደረጋቸው ጥያቄ ምን ነበር?

ማክሰኞ 5 ሜይ 2026 ጥዋት 10:18:06
የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሱዳን ጦር “ከኢትዮጵያ የተነሱ ድሮኖች ጥቃት ፈጽመዋል” በሚል ያቀረበውን ክስ “መሠረተ ቢስ” እና “በውጭ ኃይሎች ትዕዛዝ የቀረበ” ሲል ውድቅ አደረገ። ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ በምላሹ ሱዳን “ለተለያዩ ፀረ ኢትዮጵያ ኃይሎች ማዕከል” መሆኗን እንዲሁም የአገሪቱ ጦር “የህወሓት ቅጥረኛ ተዋጊዎችን እየተጠቀመ” መሆኑን በመግለጽ ከስሷል።

ማክሰኞ 5 ሜይ 2026 ጥዋት 8:25:08
የሱዳን ጦር ከኢትዮጵያ ባሕር ዳር ከተማ የተነሳ ድሮን በትናንነው ዕለት የኻርቱም ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ላይ ጥቃት አድርሷል ሲል ከሰሰ። “የተፈጸመው ቀጥተኛ ጥቃት በዝምታ አይታለፍም” ያለችው ሱዳን፤ በኢትዮጵያ የሚገኙትን አምባሳደሯን ለምክክር መጥራቷን አስታውቃለች።

ሰኞ 27 ኤፕሪል 2026 ጥዋት 4:22:02
ትናንት እሁድ በለንደን የተካሄደው የማራቶን ውድድር ኬንያዊው ሳባስቲያን ሳዌ እና ኢትዮጵያዊው ዮሚፍ ቀጄልቻ ከሁለት ሰዓት በታች ተከታትለው በመግባት ዓለምን አስደምመዋል።

ቅዳሜ 18 ኤፕሪል 2026 ጥዋት 4:48:56
ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ባለፉት 25 ዓመታት ውስጥ ስድስት የሙዚቃ አልበሞችን ለአድናቂዎቹ አድርሷል። ቴዲ በእነዚህ ዓመታት ሁሉ ልባቸው እንደ ሰም የሚቀልጥባቸው አድናቂዎች፣ ፊታቸው በመከፋት የሚጠይምባቸው ተቺዎችን አፍርቷል። ኢትዮጵያዊነት እንዴት ይገፋ ለሚልላቸው የነጻነት እና የመብት ፊታውራሪ እንዲሁም የዘመኑ ድምጽ ሲሆን ልባቸው ለሚጎሽባቸው ደግሞ ድምጻዊ ብቻ ነው። የቴዲ አፍሮን ሙዚቃዎች ምን ለየት ያደርጋቸዋል? የዘመኑ መነጋገሪያስ ለምን ሆነ? ቢቢሲ አማርኛ ባለሙያዎችን አነጋግሯል።

ዓርብ 17 ኤፕሪል 2026 ጥዋት 3:57:23
በተለምዶ የጅቦች ስም የሚነሳው ከክፉ ነገር ጋር ተያይዞ ነው። ጅቦችን ማጉረስ ባህል ከሆነበት የኢትዮጵያ ምሥራቃዊ ክፍል ውጭ ስለ ጅቦች ያለው አመለካከት ተመሳሳይ ነው ማለት ይቻላል። በመቀለ ዩኒቨርስቲ እና በዩናይትድ ኪንግደም በሚገኘው የሼፊልድ ዩኒቨርስቲ ተመራማሪ የሆኑት ዶ/ር ግደይ ይርጋ ግን የተለየ ዕይታ አላቸው። ጅቦች የካንበን ልቀትን ይቀንሳሉ፤ አካባቢን በማጽዳት ከበሽታ ይከላከላሉ፤ ገንዘብም ይቆጥባሉ ቢባል ብዙዎች ያምኑ ይሆን?

ሐሙስ 16 ኤፕሪል 2026 ጥዋት 9:41:02
“ትናንሽ አገራት” ወሳኝ የባሕር መተላለፊያዎችን “መጠበቅ ስለማይችሉ” እንደ ኢትዮጵያ አይነት “አቅም ያላቸው” አገራት ሊሳተፉ እንደሚገባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ የባሕር በር ጉዳይ “በተቻለ መጠን በሰላም” ሊፈታ የሚገባ፤ ነገር ግን “የግድ መሆን ያለበት” ጉዳይ እንደሆነ ገልጸዋል።

ረቡዕ 1 ኤፕሪል 2026 ጥዋት 3:57:30
የዓለም 20 በመቶ ነዳጅ መተላለፊያ የሆነው የሆርሙዝ ወሽመጥ በመዘጋቱ የተከሰተው የነዳጅ እጥረት በኢትዮጵያ ዋና ዋና ከተሞች የትራንስፖርት ዘርፍ ላይ ጫና ማሳደሩን ቢቢሲ ተመልክቷል። ከሰሞኑ ደግሞ በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ መኪና ዋጋ እስከ ግማሽ ሚሊዮን ብር መድረሱ ተሰምቷል። ይህ ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ ከኢራን ጦርነት ጋር ይያያዝ ይሆን?

ረቡዕ 8 ኤፕሪል 2026 ጥዋት 4:01:04
ኢራን በአሜሪካ እና በእስራኤል እየተፈጸመባት ባለው ጥቃት ከጠቅላይ መሪዋ ከአያቶላህ አሊ ኻሜኒ ጀምሮ በርካታ ቁልፍ ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ መሪዎቿ ተገድለውባታል። ነገር ግን አመራሯ ሳይፈረካከስ እየተተካካ ፍልሚያውን ቀጥሏል። ለመሆኑ የኢራን አመራር በዚህ ጦርነት ውስጥ ባለበት ጸንቶ እንዴት ሊቀጥል ቻለ?

ማክሰኞ 7 ኤፕሪል 2026 ጥዋት 3:54:22
የቅንጦት እና የንግድ መናኸሪያዎች ሆነው የቆዩት የባሕረ ሰላጤው አገራት ቅንጡ ከተሞች በኢራን ላይ የተከፈተውን ጦርነት ተከትሎ ገጽታቸው እየተቀየረ ነው። አገራቱ በጦርነቱ ዳር ላይ የቆሙ ቢሆንም በየዕለቱ የኢራን ሚሳዔሎች እየጎበኟቸው ነው። ይህ ጦርነት በወደፊት ገጽታቸው ላይ ምን ውጤት ይኖረዋል?

ረቡዕ 11 ማርች 2026 ጥዋት 12:00:00
አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ ጥቃት መክፈታቸውን ተከትሎ በመካከለኛው ምሥራቅ ውስጥ ጦርነት እየተካሄደ ነው። ኢራን እየተፈጸመባት ላለው ጥቃት አጸፋውን በቀጣናው ባሉ የአሜሪካ ወዳጅ አገራት ላይ እየፈጸመች ነው። ለዚህ ደግሞ ኢራን ርካሽ እና ውጤታማ የሆኑትን ሻሂድ-136 የተባሉ አጥፍቶ ጠፊ ድሮኖችን በስፋት እየተጠቀመች ነው። ይህ በምሥል እና በቪዲዮ የተደገፈው ዘገባ ስለድሮኖቹ ምንነት ይተነትናል።

ዓርብ 3 ኤፕሪል 2026 ጥዋት 4:02:30
በአፍሪካ ቀንድ ውስጥ የጎላ ሚና ያላት ኤምሬትስ የኢራን ጥቃት ዋነኛ ዒላማ በመሆኗ ትኩረቷን እራሷን መከላከል ላይ አድርጋለች። ይህ ሁኔታ በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል የተከሰተው ውጥረት ወደ ጦርነት እንዳያመራ አዘግይቶት ይሆን? ኢራንን ደግፈው ወደ ጦርነት የገቡት የየመን ሁቲዎች የቀይ ባሕር መግቢያን ለመዝጋት እየዛቱ ሲሆን፣ ይህ ሁኔታ ለኢትዮጵያ እና ለሌሎች አፍሪካ ቀንድ አገራት ምን ስጋት ይፈጥራል?

ማክሰኞ 24 ማርች 2026 ጥዋት 4:02:11
ኢራን በሕንድ ውቅያኖስ ዲያጎ ጋርሲያ ደሴት ላይ ወደሚገኘው የዩናይትድ ኪንግደም (ዩኬ) እና የአሜሪካ የጋራ ወታደራዊ ሰፈር ላይ የረዥም ርቀት ባለስቲክ ሚሳዔሎችን ማስወንጨፏ በመካከለኛው ምሥራቅ ያለውን ግጭት እየተባባሰ መምጣቱን ያሳያል። በእርግጥ ሚሳዔሎቹ ወደታቀደላቸው ዒላማ ሳይደርሱ ቀርተዋል። ነገር ግን የእስራኤል የመከላከያ ሠራዊት ጦርነቱ ከተጀመረ ወዲህ እንዲህ ዓይነት የረዥም ርቀት ሚሳዔሎች ጥቅም ላይ ሲውሉ ይህ የመጀመሪያው እንደሆነ ተናግሯል።

ሰኞ 23 ማርች 2026 ጥዋት 4:11:51
ዩናይትድ ስቴትስ በመካከለኛው ምሥራቅ ወደ ጦርነት ተመልሳለች። ዋሽንግተን በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ በቀጣናው በተካሄዱ ጦርነቶች ውስጥ በተለያዩ ጊዜያት የተሳተፈች ሲሆን፣ ሁሉም ያመጡት ውጤት ላይ በአንድ ድምጽ ከስምምነት መድረስ አይቻልም። በተለይ ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት በመካከለኛው ምሥራቅ እና በሰሜን አፍሪካ ያደረገቻቸው ወታደራዊ ጣልቃ ገብነቶች ምን ውጤት አስገኙ?

ሐሙስ 26 ማርች 2026 ጥዋት 4:05:53
አንድ ወር ሊሞላው በተቃረበው ጦርነት ከሞላ ጎደል አብዛኞቹ የኢራን ቁልፍ ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ መሪዎች ተገድለዋል። ነገር ግን ኢራን ከአሜሪካ እና ከእስራኤል ጋር የምታደርገውን ፍልሚያ እንዲሁም በመካከለኛው ምሥራቅ አገራት ላይ የምትፈጽመውን ጥቃት ቀጥላለች። ከከባድ ውድመት እና የመሪዎቿ ግድያ በኋላ ኢራን በእነማን እየተመራች ነው?

ረቡዕ 18 ማርች 2026 ጥዋት 3:45:42
አሜሪካ እና እስራኤል ኢራን ላይ ጥቃት ከፍተው ቴህራን ያለአጋር ብቻዋን ሁለቱን ኃያላን እየተጋፈጠች ነው። በዚህ ጊዜ በኢራን የሚደገፈው እና በቀይ ባሕር ላይ ዋነኛ ስጋት የሆነው የየመኑ ታጣቂ ቡድን ሁቲ ባልተለመደ መልኩ እራሱን ያቀበ ይመስላል። እስራኤል በሐማስ ላይ ጥቃት ስትከፍት ፈጥኖ ምላሽ የሰጠው ሁቲ ኢራን ስትጠቃ ለምን ዝምታን መረጠ?

ሰኞ 16 ማርች 2026 ጥዋት 4:02:13
ወታደራዊ ጥቃት የመፈጸም ኃይልን የተመለከቱ ውይይቶች በሚነሱባቸው ወቅቶች አሜሪካ እና እስራኤል እንዴት ኢራንን እያጠቁ እንደሆነ በምሥል ጭምር ከማሳየት ወደ ኋላ አይሉም። በባለሙያ የተዘጋጁ ፎቶዎች እና ቪዲዮዎችን የሚጠቀመው የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ፤ ጥቅም ላይ እየዋሉ ያሉ የመሣሪያ፣ የጄት እና የመርከብ ዓይነቶችን የሚያሳዩ ልጥፎችን በየአጭር ሰዓት ልዩነት ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ይለጥፋል።

ረቡዕ 4 ማርች 2026 ጥዋት 4:35:18
አሜሪካ እና እስራኤል በፈጸሙት ጥቃት የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሜኒ ሲገደሉ፤ ኢራን በመካከለኛው ምሥራቅ አገራት ላይ ጥቃት መፈጸም ቀጥላለች። እየተካሄደ ስላላው ጦርነት፣ ስለ ኢራን እና ባለፉት ቀናት ስለተከሰቱ ዋና ዋና ነገሮች ሊያውቋቸው የሚገቡ እውነታዎች በምሥል እዚህ ይመልከቱ።

ቅዳሜ 2 ሜይ 2026 ጥዋት 4:49:46
በረከት በቀለ፣ ኪምቢፊዳ በሚል ስም ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ይታወቃል። ወደ ቲክቶክ ብቅ ከማለቱ አስቀድሞ “በስፓይና ቢፊዳ (spina befida) የተያዝኩ ብቸኛው ሰው እኔ ብቻ እንደሆንኩ ይሰማኝ ነበር” ይላል። የአሊያንስ ፎር በርዝ ዲፌክት መሥራቹ ዶ/ር ነቢያት ተስፋዬም ልክ እንደ በረከት ሁሉ ከስፓይና ቢፊዳ (የነርቭ ዘንግ ክፍተት) ጋር ነው የተወለደው። አሁን 33 ዓመት እንደሆነው የሚናገረው ዶ/ር ነቢያት፣ በተወለደ በ22ኛው ቀን የስፓይና ቢፊዳ የቀዶ ሕክምና ተደርጎለታል። ሁለቱም ወጣቶች ከራሳቸው ህመም ተነስተው ሕክምና ለማጥናት መወሰናቸውን ለቢቢሲ ተናግረዋል።

እሑድ 26 ኤፕሪል 2026 ጥዋት 5:04:36
በመኪና፣ በባቡር አልያም በአውሮፕላን መጓዝ የሚያስጨንቃቸው ብዙዎች ናቸው። ሕመሙን መቋቋም ስለማይችሉ ረዥም ጉዞ የማያደርጉ አሉ። ሌሎች ደግሞ ራሳቸውን ለማከም ይሞክራሉ።ለመሆኑ ይህን ሕመም የሚያስከትለው ምንድን ነው? እንዴት ማከምስ ይቻላል?

እሑድ 26 ኤፕሪል 2026 ጥዋት 5:05:23
ጨው ምግባችንን የበለጠ ያጣፍጠዋል። ለሰው ልጅ ሕይወትም አስፈላጊ ነው። በጨው ውስጥ የሚገኘው ሶዲየም በሰውነት ውስጥ የሚኖረውን ትክክለኛውን የውሃ መጠን ለመጠበቅ በጣም አስፈላጊ ነው። ህዋሳትም ንጥረ ምግቦችን እንዲወስዱ ይረዳል። በምግብ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩረው የቢቢሲ ወርልድ ሰርቪስ ፕሮግራም “ዘ ፉድ ቼይን” ጨው በሰውነታችን ውስጥ ያለውን ወሳኝ ሚና እና ለአንድ ሰው ከመጠን በላይ የሚባለው የጨው ፍጆታ ምን ያህል ነው የሚለውን ተመልክቷል።

ዓርብ 26 ዲሴምበር 2025 ጥዋት 4:02:06
ስኪዞፍሪኒያ የሚባል የአእምሮ ጤና መታወክ እንዴት ያለ ነው? ፕሮፌሰር ሰለሞን ተፈራ ፒኤችዲ ሠርተውበታል። ለ20 ዓመት ተመራምረውበታል። በስኪዞፍሬኒያ የሚሰቃዩ በርካታ ታካሚዎች ነበሯቸው፤ አሏቸው። ፕሮፌሰሩ ነገርን በአጭር የማስረዳት ፀጋ አላቸው። ይህን የአእምሮ በሽታ እንዲህ ይገልጹታል። “ነገሩ የማርያምን ብቅል ሲፈጩ መዋል ነው” ይሉታል። ምን ማለታቸው ነው?

ሐሙስ 2 ኤፕሪል 2026 ጥዋት 3:55:06
በእንቅልፍ እጦት ተቸግረዋል? በተቆራረጠ እንቅልፍ ምክንያት የተረበሸ ሌሊት ያሳልፋሉ? በዚህ ምክንያትስ የቀን ውሎዎ በድካም የተሞላ ነው? ጥናቶች ከእንቅልፋችን ስንነሳ ጥሩ ስሜት የመሰማቱ ምሥጢር የሚጀምረው ከቀን ውሏችን ነው ይላሉ።

ዓርብ 27 ማርች 2026 ጥዋት 3:59:27
የዓለም ጤና ድርጅት በአውሮፓውያኑ በ2021 ባወጣው አሃዝ መሠረት በመላው ዓለም ከ127 ሰዎች መካከል አንዳቸው ኦቲዝም እንዳለበት/እንዳለባት ያሳያል። አነስተኛ እና መካከለኛ ገቢ ባላቸው አገራት በቂ መረጃ ባይገኝም፤ ለአእምሮ ዕድገት መዛባት ያለው ተጋላጭነት በየአገሩ የተለያየ መሆኑ ተስተውሏል።

ረቡዕ 18 ማርች 2026 ጥዋት 3:47:37
እንሰት በኢትዮጵያ ለ20 ሚሊዮን ሰዎች በምግብነት ያገለግላል። ይህም ከአጠቃላዩ ሕዝብ 15 በመቶው ነው። እንሰት ድርቅን ለመቋቋም ካለው ተፈጥሯዊ አቅ ምአንጻር ‘ረሃብ የሚዋጋው ዛፍ’ እንዲሁም ሙዝን ስለሚመስል ‘የውሸት ሙዝ’ የሚሉ ስያሜዎችን አግኝቷል።

እሑድ 15 ፌብሩዋሪ 2026 ጥዋት 4:55:55
በመቶዎች ከሚቆጠሩ ዓመታት በኋላ ደጋፊዎቹ ሁለቱንም የዓለም ጦርነቶች፣ የሂሮሺማ እና የናጋሳኪ የኒውክሌር ፍንዳታዎችን፣ የሂትለርን መነሳት እና የኮቪድ-19 ወረርሽኝን ጨምሮ ብዙ ታሪካዊ ክስተቶችን፣ ምንም እንኳን እነዚህን ክስተቶች በስም ባይጠቅሳቸውም እንደተነበየ ይናገራሉ።

ሐሙስ 5 ማርች 2026 ጥዋት 4:05:05
በአውሮፓውያኑ ጥር 25/1995 ኖርዌይ ‘ኖርዘርን ላይትስ’ የተባለውን የሰማይ ላይ ደማቅ ብርሃን ለማጥናት የተኮሰችውን ሮኬት ሩሲያ በስህተት ወደ ሞስኮ የተወነጨፈ የኒውክሌር ሚሳዔል እንደሆነ ቆጥራው ነበር። ከቀዝቃዛ ጦርነት ስሜት ገና በቅጡ ያላገገመው ዓለም በአንድ የአዘቦት ቀን ለሰዓታት የቆየ በድጋሚ ጦርነት ውስጥ የመግባት አስከፊ ስጋት ተጋርጦባት ነበር።

እሑድ 1 ፌብሩዋሪ 2026 ጥዋት 4:39:15
የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ ሳይንስ እና ባህል ተቋም በዓለም የማይዳሰሱ ቅርሶች ዝርዝር ውስጥ ኩልን አካቶታል።

ቅዳሜ 2 ሜይ 2026 ጥዋት 4:49:46
በረከት በቀለ፣ ኪምቢፊዳ በሚል ስም ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ይታወቃል። ወደ ቲክቶክ ብቅ ከማለቱ አስቀድሞ “በስፓይና ቢፊዳ (spina befida) የተያዝኩ ብቸኛው ሰው እኔ ብቻ እንደሆንኩ ይሰማኝ ነበር” ይላል። የአሊያንስ ፎር በርዝ ዲፌክት መሥራቹ ዶ/ር ነቢያት ተስፋዬም ልክ እንደ በረከት ሁሉ ከስፓይና ቢፊዳ (የነርቭ ዘንግ ክፍተት) ጋር ነው የተወለደው። አሁን 33 ዓመት እንደሆነው የሚናገረው ዶ/ር ነቢያት፣ በተወለደ በ22ኛው ቀን የስፓይና ቢፊዳ የቀዶ ሕክምና ተደርጎለታል። ሁለቱም ወጣቶች ከራሳቸው ህመም ተነስተው ሕክምና ለማጥናት መወሰናቸውን ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ሰኞ 27 ኤፕሪል 2026 ጥዋት 4:22:02
ትናንት እሁድ በለንደን የተካሄደው የማራቶን ውድድር ኬንያዊው ሳባስቲያን ሳዌ እና ኢትዮጵያዊው ዮሚፍ ቀጄልቻ ከሁለት ሰዓት በታች ተከታትለው በመግባት ዓለምን አስደምመዋል።

እሑድ 26 ኤፕሪል 2026 ጥዋት 5:05:23
ጨው ምግባችንን የበለጠ ያጣፍጠዋል። ለሰው ልጅ ሕይወትም አስፈላጊ ነው። በጨው ውስጥ የሚገኘው ሶዲየም በሰውነት ውስጥ የሚኖረውን ትክክለኛውን የውሃ መጠን ለመጠበቅ በጣም አስፈላጊ ነው። ህዋሳትም ንጥረ ምግቦችን እንዲወስዱ ይረዳል። በምግብ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩረው የቢቢሲ ወርልድ ሰርቪስ ፕሮግራም “ዘ ፉድ ቼይን” ጨው በሰውነታችን ውስጥ ያለውን ወሳኝ ሚና እና ለአንድ ሰው ከመጠን በላይ የሚባለው የጨው ፍጆታ ምን ያህል ነው የሚለውን ተመልክቷል።

ሰኞ 20 ኤፕሪል 2026 ጥዋት 4:06:14
አሜሪካ ወደ ኢራን ወደቦች የሚገቡ እና የሚወጡ መርከቦች ላይ እገዳ መጣሏ ጥንታዊ የወታደራዊ ጫና መፍጠሪያ ስልትን መልሶ ያመጣ ነው። ይህ እርምጃ የባሕር መስመሮችን በመዝጋት ምጣኔ ኃብታዊ ጫና መፍጠር፣ ንግድን ማስተጓጎል እና ተገዳዳሪው አካል አቋሙን እንዲቀይር ወይም እጅ እንዲሰጥ የማስገደጃ ስልት ነው። ታሪክ የሚያሳየን እንዲህ ዓይነት ስልቶች ጫና በመፍጠር ረገድ ውጤታማ ቢሆኑም ሰፊ ተጽዕኗቸው ግን ከሚታሰበው በላይ ውስብስብ መሆኑን ነው።