ረቡዕ 20 ኦገስት 2025 ጥዋት 7:38:52
የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን ባልታወቀ ቡድን ታግቶ በተፈጸመበት ድብደባ ሕይወቱ ያለፈውን የቀይ መስቀል ባልደረባ ሆነልኝ ፋንታሁንን “አሰቃቂ ህልፈት” አወገዘ። “የረድዔት ሠራተኞች የጥቃት ዒላማ ሊሆኑ አይገባም” ሲሉ በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ (ኦቻ) ጊዜያዊ አስተዳዳሪ ዶክተር አቡባካር ካምፖ መናገራቸውን ቢሮው ገልጿል።
ማክሰኞ 19 ኦገስት 2025 ጥዋት 11:08:54
የኢትዮጵያ መንግሥት ተጨማሪ እሴት ታክስን (ቫት) ወደ 17.5 በመቶ እንዲያሳድግ ቀረበለትን ምክረ ሀሳብ ተግባራዊ እንደማያደርግ ጠቆመ። መንግሥት በዚህ ዓመት አዋጁን ሲያሻሽል የተጨማሪ እሴት ታክስ ምጣኔ 15 በመቶ ሆኖ እንዲቀጥል” መወሰኑን የገንዘብ ሚኒስቴር ገልጿል። የፌደራል መንግሥት ይህንን ውሳኔ ያስተላለፈው ቫትን አሁን ካለበት “15 በመቶ ከፍ እንዲል ማድረግ ጫና” ሊፈጥር እንደሚችል የቀረበለትን ምክረ ሀሳብ በመቀበል መሆኑን ገልጿል።
ማክሰኞ 19 ኦገስት 2025 ጥዋት 10:59:44
በደቡብ ትግራይ በራያ አዘቦ ወረዳ መኾኒ ከተማ የክልሉ ፀጥታ ኃይሎች ከነዋሪዎች ጋር የፈጠሩትን ግጭት ተከትሎ በከፈቱት ተኩስ በርካታ ሰዎች መቁሰላቸውን ቢቢሲ ትግርኛ ከነዋሪዎች፣ ከቤተሰቦች እና ከሕክምና ባለሙያዎች ሰምቷል። ጥቃቱ የተፈጸመው በትግራይ “አርሚ 43” ዕዝ አባላት በአካባቢው በተሰማሩበት ጊዜ በተፈጠረ አለመግባባት ግጭት ተፈጥሮ በወሰዱት እርምጃ መሆኑን የዓይን እማኞች ይናገራሉ።
ማክሰኞ 19 ኦገስት 2025 ጥዋት 7:05:43
ለረዥም ጊዜ በተለያዩ መድረኮች አብሮት የሠራው ፀሐፌ ተውኔት አያልነህ ሙላቱ፣ ደበበን ሲያስታውሰው “የኪነጥበብ ሕይወታችን ለውጭው ዓለም ካስተዋወቁልን የጥበብ ሰዎች መካከል አንዱ” ይለዋል። በምርጫ 97 ዋነኛ የፖለቲካ ተፎካካሪ የነበረው ቅንጅት ለአንድነት ለዲሞክራሲ ፓርቲ ውስጥ አባል የነበረችው እና አብራው የተለያዩ የፖለቲካ ሥራዎችን የሠራችው ብርቱካን ሚደቅሳ ደግሞ “ፖለቲካን ከተለመደው መልኩ በተለየ መንገድ መሥራት የቻለ” ስትል ያላትን አክብሮት ትገልጻለች።
ማክሰኞ 19 ኦገስት 2025 ጥዋት 4:00:21
ባለፉት ዓመታት እየተዳከመ ከዋና ዋና ከተሞች ውጪ በመሆን ላይ የነበረው እና ከአል-ቃኢዳ ጋር ግንኙነት እንዳለው የሚነገርለት ታጣቂው የሶማሊያ ቡድን አልሻባብ እያንሰራራ ነው። በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ ኅብረት ኃይሎች ድጋፍ ከዓመታት በፊት ከቡድኑ ነጻ የሆኑ አካባቢዎችን ከመንግሥት ኃይሎች ነጥቆ በመቆጣጠር ላይ ነው። የሶማሊያ መንግሥት ፖለቲካዊ አለመረጋጋት አልሻባብን እንዲጠናከር እያደረገው መሆኑን ተንታኞች ይናገራሉ።
ሰኞ 18 ኦገስት 2025 ጥዋት 7:31:55
የፌደራል መንግሥት ከአንድ ዓመት በኋላ በድጋሚ ይፋ ባደረገው ደመወዝ ማሻሻያ 6,900 ብር የነበረው የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው የመንግሥት ሠራተኞች መነሻ ደመወዝ ወደ 11,500 ብር ከፍ አለ።በአዲሱ ማሻሻያ፤ ዝቅተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ላይ የ1,240 ብር ጭማሪ የተደረገ ሲሆን፣ ከፍተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ደግሞ በ17,508 ብር እንዲያድግ ተደርጓል።
እሑድ 17 ኦገስት 2025 ጥዋት 10:39:51
ከጠፋ ሳምንት ገደማ የሆነው ጋዜጠኛ አብዱልሰመድ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ሆኖ ቢታይም የት እንደታሰረ እንዳልታወቀ እንዲሁም ጠበቃም ሆነ ቤተሰቡም እንዲያገኝ እንዳልተደረገ ተገልጿል። ረዕቡ ዕለት “ጭንብል የለበሱ እና የወታደር ዩኒፎርም ያደረጉ በሚመስሉ” ሰዎች ተወስዷል የተባለው ጋዜጠኛ ዮናስ ደግሞ፤ ያለበትም ሆነ በየትኛው አካል እንደተወሰደ በትክክል አለመታወቁን የሪፖርተር ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ለቢቢሲ ተናግሯል።
ዓርብ 15 ኦገስት 2025 ጥዋት 9:11:39
በትግራይ ክልል በሽረ አቅራቢያ በምትገኘው እንዳባጉና ከተማ ከሰሞኑ የሰባት ዓመት ልጅ ታግቶ ተገድሎ መጣሉ የከተማዋን ነዋሪዎች እና የማህበራዊ ሚዲያዎች ተጠቃሚዎችን በከፍተኛ ሁኔታ አስደንግጧል። ናዖድ ተክላይ ብርሃነ የተሰኘው የሰባት ዓመቱ ሕጻንን ያገቱት ግለሰቦች ለማስለቀቂያ ከእናቱ 600 ሺህ ብር ከተቀበሉ በኋላ ልጁን ገድለው ድልድይ ላይ የጣሉት ባለፈው ሳምንት ነው።
ረቡዕ 13 ኦገስት 2025 ጥዋት 9:22:38
የኢትዮጵያ መንግሥት ኃይሎች እና ታጣቂዎች በዜጎች ላይ “ከሕግ ውጪ የሆኑ ግድያዎች” መፈጸማቸውን የሚያሳዩ “ታማኝ መረጃዎች” መኖራቸውን የአሜሪካ መንግሥት ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ትግበራ ሪፖርት አመለከተ።
ሐሙስ 14 ኦገስት 2025 ጥዋት 8:27:58
ሠራዊታቸው በጋዛ ውስጥ በሚያካሂደው ጦርነት ምክንያት በተፈጠረው የሰላማዊ ሰዎች ሞት እና ረሃብ ከፍተኛ ትችት እና ተቃውሞን ከወዳጆቻቸው ሳይቀር እየደረሰባቸው የሚገኙት የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታኒያሁ ሌላ ተቃውሞ ተቀስቅሶባቸዋል። ባለፈው ማክሰኞ አይ24 ከተባለው የአገራቸው ቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር ባደረጉት ቆይታ የሰጡት አስተያየት በበርካታ የአረብ አገራት ዘንድ ቁጣን ከመቀስቀሱ በተጨማሪ ማብራሪያ እንዲሰጡ እየተጠየቁ ነው።
ረቡዕ 13 ኦገስት 2025 ጥዋት 10:20:33
የግብፁ ፕሬዚዳንት አብደል ፋታህ አል ሲሲ አገራቸው በናይል (አባይ) ያላትን የውሃ ድርሻ እንዲነካ እንደማትፈቅድ አስጠነቀቁ። ፕሬዚዳንት አል ሲሲ ይህንን ያሉት ከላይኛው የናይል ተፋሰስ አገራት አንዷ ከሆነችው የኡጋንዳ ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ ጋር በካይሮ አል ኢትሃድያ ቤተ መንግሥት ማክሰኞ፣ ነሐሴ 6/2017 ዓ.ም. በጣምራ በሰጡት መግለጫ ነው።
ማክሰኞ 12 ኦገስት 2025 ጥዋት 7:40:20
በትግራይ ኃይሎች እና ታጣቂዎች መካከል ለሁለተኛ ጊዜ ግጭት ተከስቶ የአንድ ሰው ሕይወት አልፏል። ሁለቱም ወገኖች ተፈጠረ በተባለው ጥቃት እርስ በእርስ እየተወነጃጀሉ ነው። ቢቢሲ ያነጋገራቸው የታጣቂዎቹ አዛዥ ብርጋዴር ጄነራል ገ/እግዚአብሐር በየነ የትግራይ ኃይሎች የአፋር ድንበርን አልፈው በመምጣት ጥቃት እንደከፈቱባቸው ይናገራሉ።
ሰኞ 11 ኦገስት 2025 ጥዋት 4:01:11
ሁለት ዓመት ሊሞላው በተቃረበው ጦርነት በጋዛ ሰርጥ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ሲገደሉ የግዛቲቱ አብዛኛው ክፍል ፈራርሷል። እስራኤል ዘመቻዋን ስትጀምር ያስቀመጠቻቸው ታጋቾችን የማስለቀቅ እና ሐማስን የመደምሰስ ዕቅዷ ከግቡ አልደረሰም። ከወዳጆቿ ሳይቀር ተቃውሞ ቢገጥማትም አሁን ደግሞ ጋዛን ሙሉ ለሙሉ የመቆጣጠር ዕቅድ እንዳላት ይፋ አድርጋለች። በርካታ መሪዎቹ የተገደሉበት ሐማስ ከዚህ ጦርነት በኋላ ዕጣ ፈንታው ምን ሊሆን ይችላል?
ማክሰኞ 12 ኦገስት 2025 ጥዋት 6:09:08
የኤርትራው ማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገ/መስቀል የብልጽግና ምክር ቤት አርብ ዕለት ያወጣውን መግለጫ ተከትሎ ሰኞ ነሐሴ 5/2017 ዓ.ም. አመሻሽ ላይ በኤክስ ገጻቸው ላይ ብልጽግና “በየጊዜው አሉታዊ እና ሐሰተኛ መረጃ እያሰራጨ ነው” ሲሉ ወነጀሉ።
ዓርብ 8 ኦገስት 2025 ከሰዓት 12:55:45
የብልጽግና ፓርቲ ምክር ቤት “የተራዘመ ጦርነት የተጨናገፈባቸው ጠላቶች” ሲል የገለጻቸው ኃይሎች የተለያዩ ስልቶችን በመጠቀም ኢትዮጵያ ውስጥ ግጭትን ለመቀስቀስ እየሞከሩ ነው ሲል ከሰሰ። ምክር ቤቱ “ጠላቶች” ሲል የገለፃቸውን በስም ባይጠቅስም፣ በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የሚንቀሳቀሱ “ጽንፈኞችን” በመጠቀም የሕዝብን እና የመንግሥትን አንድነት ለመከፋፈል ጥረት እያደረጉ ነው ብሏል።
ዓርብ 8 ኦገስት 2025 ጥዋት 10:19:13
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2017 በጀት ዓመት ከ28 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ያስገኙት የዳታ ማይኒንግ ኩባንያዎች ፤ “በሂደት እንዲወጡ” የማድረግ ፍላጎት እንዳለው እና ከአሁን በኋላም ለአዲስ የዳታ ማይኒንግ ኩባንያዎች ፈቃድ እንደማይሰጥ አስታወቀ።
ቅዳሜ 16 ኦገስት 2025 ጥዋት 4:36:29
ንጉሥ አርማህ ከ24 ዓመት በኋላ ዳግም ለመድረክ በቅቷል። ከፀሐፌ ተውኔት መልካሙ ዘሪሁን ብዕር አብራክ የተገኘው እና በተሻለ አሰፋ (ዶ/ር) ፊታውራሪነት የተዘጋጀው ይህ ቴአትር አጃቢ ተዋንያናዮቹን እና ተወዛዋዦቹን ጨምሮ ከ70 በላይ ተዋንያን ይሳተፉበታል። ይህ በበርካቶች ዘንድ ‘አብሮነታችንን ከፍ ያደርጋል። ዘመን ተሻጋሪ ከፍታችንንም ያሳያል’ የተባለለት ተውኔት ደራሲ እና አዘጋጁ ከቢቢሲ ጋር ቆይታ አድርገዋል።
ሐሙስ 14 ኦገስት 2025 ጥዋት 3:57:46
ያለብንን በሽታ በትክክል ለማወቅ በጣም ውድ እና ወደ ሰውነታችን ዘልቆ በመግባት ምን እየተካሄደ እንዳለ ለማወቅ የሚያስችሉ ዘመናዊ መሣሪያዎች እንደሚያስፈልጉ እናስባለን። በእርግጥ እነዚህ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተራቀቁ የህክምና መሣሪያዎች የሚሰጡት ጠቀሜታ አስገራሚ ነው። ሆኖም ያለንበትን የጤና ሁኔታ ለማወቅ የሚያስችሉ ብቸኛ ዘዴዎች አለመሆናቸውን ብንነግራችሁስ?
ቅዳሜ 9 ኦገስት 2025 ጥዋት 4:49:57
መዓዛ ወርቁ ካሉን ጥቂት ሴት ፀሐፌ ተውኔቶች መካከል አንዷ ነች። መዓዛ ከተለመደው ‘የሶፋና ግድግዳ’ ተውኔቶች ወጣ ያሉ ማኅበራዊ ፍትህን፣ ሰብዓዊትን፣ የኖረ ልማድን የሚያጠይቁ የመድረክ ተውኔቶች፣ የሬዲዮ እና የቴሌቪዥን ድራማዎችን አቅርባልናለች። በእንግሊዝኛም በአማርኛም በእኩል የመትጽፈው መዓዛ የተለያዩ ሥራዎቿን አቅርባለች። አዳዲስ ነገሮችን መሞከር መለያዋ ከሆነችው መዓዛ ጋር ቢቢሲ ቆይታ አድርጓል።
ረቡዕ 13 ኦገስት 2025 ጥዋት 3:38:02
ብዙዎቻችን የራሳችንንም ሆነ የልጆቻችንን ምሥሎች እና ቪዲዮዎችን በማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ እናጋራለን። እነዚህ በበይነ መረብ ላይ የምናስቀምጣቸው መረጃዎች አሁን አሁን ለበርካቶች ደኅንነት ስጋት ለሆነው ዲፕፌክ ግብዓት እንደሚሆን ኢትዮጵያዊው ባለሙያ ይናገራሉ።
እሑድ 10 ኦገስት 2025 ጥዋት 4:59:38
በምንመገበው፣ በምንጠጣው፣ ወይም ከምንተነፍሰው አየር ውስጥ ጥቃቅን ፕላስቲኮች በሁሉም ቦታ ይገኛሉ። ከሰውነት ፈሳሾች ከምራቅ እና ከደም እስከ አክታ እና የጡት ወተት፣ ጉበት፣ ኩላሊት፣ ጣፊያ፣ አንጎል እና አጥንታችን ውስጥ ይገኛሉ። እነዚህ ሁሉ ማስረጃዎች አንድ ጥያቄን ያጭራሉ፤ ይህ ሁሉ ፕላስቲክ በጤናችን ላይ ምን እያደረገ ነው?
ሰኞ 4 ኦገስት 2025 ጥዋት 3:42:17
የአፕል ዋና ሥራ አስፈጻሚ የነበረው ስቲቭ ጆብስ የሚመራው ኩባንያ አይፓድን ለገበያ ባቀረበበት ወቅት ልጆቹ ይህ ቴክኖሎጂ እንዲኖራቸው አልፈቀደም ነበር። ቢል ጌትስ፤ ልጆቹ ለቴክኖሎጂ ያላቸውን ቅርበት እንደገደበ ተናግሯል።
ሰኞ 4 ኦገስት 2025 ጥዋት 3:43:40
ማር ተፈጥሯዊ ማጣፈጫ ነው። ባክቴሪያዎች ደግሞ ጣፋጭ ነገር ይወዳሉ። ማር ግን ብልሽትን ተቋቁሞ ለረዥም ጊዜ ይቆያል። ማር ባክቴሪያዎችን ተቋቁሞ ለረዥም ጊዜ የመቆየት ምሥጢሩ ምንድን ነው?
ቅዳሜ 2 ኦገስት 2025 ጥዋት 4:47:15
አዲስ አበባ ተወልዳ ያደገችው ርብቃ ፍሰሃ በእንግሊዝኛ ቋንቋ ሁለት ረዣዥም ልብ ወለዶችን አሳትማለች። በሥነ ጽሑፍ የበኩር ሥራዋ ኢትዮጵያዊነትን የሚያጎላ ተውኔት መሆኑን ትናገራለች። የርብቃ አጫጭር ልብ ወለዶች፣ ወጎች እና መጣጥፎች በተለያዩ የሕትመት ውጤቶች ላይ ታትመው ለአንባቢ ደርሰዋል።
ሐሙስ 31 ጁላይ 2025 ጥዋት 3:58:51
ምንም እንኳ ረዥም ዓመት በጉዳዩ ላይ ጥናት እና ምርምር ቢካሄድም የዚህ መንስዔ ይህ ነው ብሎ ማመልከት አልተቻለም። የሕክምና ባለሙያዎች በወሊድ ወቅት በድንገት የሚከሰት የሆርሞን ለውጥ ሊሆን ይችላል ሲሉ ግምታቸውን ያስቀምጣሉ።
ማክሰኞ 22 ጁላይ 2025 ጥዋት 4:02:12
ስማችሁን ሊያጠፋ ይችላል። ባህሪያችሁን የመሸርሸር አቅም አለው። ያዝናናል። በብዙዎች ዘንድ ግን “ኃጢያት” ነው። ሐሜት ከገጠር እስከ ከተማ በአብዛኛው ማኅበረሰብ ባህል ውስጥ የሚስተዋል ባህሪ እንደሆነ ተመራማሪዎች ይናገራሉ። በዋሽንግተን ስቴት ዩኒቨርስቲ የዝግመተ ለውጥ ተመራማሪ እና ተባባሪ ፕሮፌሰር የሆኑት ዶ/ር ኒኮል ሄገን ሄስ “ከሁኔታዎች አንፃር ሁሉም ሰው በየትኛውም ባህል ሊያማ ይችላል” ይላሉ።
ረቡዕ 23 ጁላይ 2025 ጥዋት 3:55:10
የዘረ መል ምህንድስና በሰውነት ውስጥ ችግር የገጠመውን ዘረ መል አስወግዶ በሌላ ዘረ መል መተካት፣ ጤናማ ያልሆነን የዘረ መል ክፍል ቆርጦ ማውጣት፣ ወደ ሰውነት ጤናማ ዘረ መል ማከል እና ወደ ሰውነት ማስገባት ዋነኛ የዘረ መል ምህንድስና ዓይነቶች ናቸው። የዘረ መል ምህንድስና ምንድን ነው? የሕክምናውን ዘርፍስ እንዴት እየለወጠ ይገኛል? በሚለው ዙሪያ የዘረ መል ምህንድስና ተመራማሪው ዶ/ር ጆቴ ታፈሰ ከቢቢሲ ጋር ቆይታ አድርገዋል።
ረቡዕ 6 ኦገስት 2025 ጥዋት 7:09:00
በፋሽን ኢንዱስትሪው ስመ ጥር የሚባለው ታዋቂው የአልባሳት አምራች ዛራ ሁለት ማስታወቂያዎች “ጤናማ የማይመስሉ የከሱ” ሞዴሎችን በመጠቀሙ ታገዱ።
ረቡዕ 23 ጁላይ 2025 ጥዋት 10:41:34
በደምቢዶሎ ከተማ በሁለተኛ ዲግሪ (ማስተርስ) ተመርቃ መንገድ ላይ አትክልት እና ፍራፍሬ በመቸርቸር የምትተዳደረው መምህርት ፎቶ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ተጋርቶ በርካቶች ዘንድ አነጋጋሪ ሆኗል።
ዓርብ 4 ጁላይ 2025 ጥዋት 4:04:59
የቦዲ ማኅበረሰቦች አዲስ ዓመታቸውን የሚያከብሩት አዳዲስ ልብሶችን በመግዛት፣ የቤት እቃቸውን በመቀየር አይደለም - ለወራት በመቀለብ እንጂ። ቦዲዎች አዲስ ዓመታቸውን ‘ከኤል’ ይሉታል።ከኤል የተለየ ትርጉም የለውም። የዘመን መለወጫ ወይም ልዩ የአዲስ ዓመት ክብረ በዓል ማለት ነው። ለክብረ በዓሉ የሚዘጋጁትም ከበዓሉ ሁለት ወይም ሦስት ወራት ቀደም ብለው በመቀለብ ነው።
ሰኞ 28 ጁላይ 2025 ጥዋት 3:57:32
በወንጀል ዓለም ውስጥ በጣም የሚፈራው የአልካታራዝ እስር ቤት ደሴት ላይ ተገነባ ነው። “ዘ ሮክ” የሚል ቅጽል ስም ተሰጥቶት የነበረው የፌዴራል ማረሚያ ቤት በአሜሪካ በጣም አደገኛ ወንጀለኞችን የሚታሰሩበት ነበር። እነዚህ ደጋጋሚ ወንጀለኞች፣ ረዥም የሽቦ አጥር፣ ስድስት የመቆጣጠሪያ ማማ ያሉትን በባሕር የተከበበ ጥብቅ እስር ቤትን እንዴት ጥሰው ወጡ?
እሑድ 20 ጁላይ 2025 ጥዋት 9:16:31
የኢንዶኔዥያ ፖሊስ ከ2023 ጀምሮ በሲንጋፖር ቢያንስ 25 ጨቅላ ሕፃናትን ሸጧል የተባለውን ዓለም አቀፍ ሕገ ወጥ የሕጻናት አዘዋዋሪ ቡድን አገኘ።
ሰኞ 28 ጁላይ 2025 ጥዋት 7:47:12
ማሱድ ፔዜሽኪያን ሐምሌ 2024 የኢራን ፕሬዝዳንት ሆነው ከተሾሙ ከአንድ ቀን በኋላ በቀጥታ ወደ ፖለቲካ እሳት ውስጥ ገብተዋል። ይህም አለመረጋጋት በሌለው በኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ መሪዎች ታሪክ ውስጥ ከታዩት ጅማሪዎች መካከል እጅግ አስደንጋጩ እና በቀውስ የታጀበ ነበር።
ማክሰኞ 15 ጁላይ 2025 ጥዋት 3:46:01
ዩናይትድ ስቴትስ የመጀመሪያውን የኒውክሌር ቦምብ ካፈነዳች ከሰማንያ ዓመታት በኋላ የኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር የመካከለኛው ምሥራቅን ወደ ግጭት ቀጣና እየቀየረው ነው።በአሁኑ ጊዜ በዓለም ላይ ዘጠኝ አገራት የኒውክሌር ጦር መሳሪያ እንዳላቸው ይታወቃል። እንዴት የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ሊታጠቁ ቻሉ? ሌሎች አገራትስ መሣሪያውን ማግኘት ከፈለጉ ይህንን ማሳካት ይችላሉ?
ቅዳሜ 5 ጁላይ 2025 ጥዋት 4:41:59
ባለፉት በርካታ አስርት ዓመታት ምዕራባውያን በአሜሪካ እየተመሩ በተለያዩ አገራት በተለይም ውጥረት በማይለየው መካከለኛው ምሥራቅ ውስጥ ታልቃ ገብተዋል። በዚህም ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ እና ወታደሮቻቸውን እንዲሁም ፖለቲከኞቻቸውን በማሳተፍ እነሱ ስጋት ወይም ችግር ያሉትን “ለመፍታት” ጣልቃ ገብተዋል። ይህ ዘገባ አሜሪካ በመካከለኛው ምሥራቅ ያደረገቻቸውን አራት ጣልቃ ገብነቶችን በማንሳት ገምግሟል።
ማክሰኞ 1 ጁላይ 2025 ጥዋት 3:57:49
በአውሮፓውያኑ መጋቢት 5/1957 ዩናይትድ ስቴትስ በወቅቱ በመሐመድ ሬዛ ፓህላቪ ከምትመራው ኢራን ጋር ለሲቪል የአውቶሚክ ኢነርጂ አጠቃቀም የትብብር ስምምነት ተፈራረመች። በ’አተምስ ፎር ፒስ’ መርሃ ግብር ጥላ ስር የነበረው ይህ ስምምነት የኢራንን የኒውክሌር መርሃ ግብር ለመጀመር መሠረት ጣለ። ለዋሽንግተን፣ በዚያ የቀዝቃዛ ጦርነት ወቅት ኢራን ተጨማሪ መስህብ ነበራት።
ሐሙስ 19 ጁን 2025 ጥዋት 3:52:56
እስራኤል ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ለአርብ አጥቢያ በፈጸመችው ጥቃት ቁልፍ የሚባሉ የኢራን የጦር አዛዦች እንዲሁም የኒውክሌር ሳይንቲስቶች መገደላቸው ያሉበትን ትክክለኛ ቦታ በተመለከተ መረጃ እንዳላት የሚያሳይ ነው። ከዚህ መረጃ እና ተልዕኮ ጀርባ ደግሞ የአገሪቱ የሥለላ ተቋም ሞሳድ እንዳለ ይታመናል። ሞሳድ ባለፉት ሰባት አስርት ዓመታት ውስጥ ከኢትዮጵያ እስከ ኢራን የፈጸማቸው ዋናዎቹ ተልዕኮዎች የትኞቹ ናቸው?
ሰኞ 23 ጁን 2025 ጥዋት 3:54:51
…የኢራን ከፍተኛ ጄነራሎች እሰራኤል ጥቃት ልትሰነዝር ትችላለች የሚለው ነገር አሳስቧቸው ስብሰባ ጠሩ። ሁልጊዜም እንደሚያደርጉት ‘የእስራኤል ነገር አይታወቅም’ ብለው ከመሬት ሥር በተዘጋጀ የምድር ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ ገቡ። ሞሳድ ግን ይህን ያውቅ ነበር። ቁልፍ ስብሰባዎች እዚህ ምድር ቤት እንደሚደረጉ መረጃ ነበረው።. . .
ሐሙስ 19 ጁን 2025 ጥዋት 3:56:12
የኢራንን ከምድር በታች የተገነቡ የኒውክሌር ተቋማትን ለመምታት የሚችለው መሳሪያ አንድ ብቻ ነው። ይህ እስካሁን ጥቅም ላይ ያልዋለው ቦምብ ደግሞ የሚገኘው በአሜሪካ እጅ ብቻ ነው። እስራኤልም ይህንን መሳሪያ እንድትጠቀም እስካሁን የአሜሪካን ይሁንታ አላገኘችም።
ዓርብ 13 ጁን 2025 ጥዋት 3:51:33
ኢራን እና እስራኤል ለረጅም ጊዜ በእጅ አዙር እንጂ በቀጥታ ግጭት ውስጥ ገብተው አየውቁም። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን አንደኛው በሌላኛው ላይ የቀጥታ ጥቃት እየፈጸሙ ከጦርነት አፋፍ ላይ መድረሳቸው አሳሳቢ ሆኗል። ለመሆኑ እስራኤል እና ኢራን ጦርነት ውስጥ ቢገቡ ምን ሊከሰት ይችላል? ሁለቱ አገራትስ በወታደራዊ አቅም ምን ያህል ይመጣጠናሉ?
እሑድ 15 ጁን 2025 ጥዋት 4:51:06
ኢራን ከግብፅ ቀጥላ ለእስራኤል እውቅና በመስጠት ሁለተኛዋ እስላማዊ አገር ነበረች። ነገር ግን ከኢራን እስላማዊ አብዮት በኋላ ይህ ግንኙነት ተበላሽቶ ከአራት አስርታት በላይ በጠላትነት እየተያዩ ቆይተዋል። ለመሆኑ የሁለቱ አገራት ግንኙነት ወደ ደመኛ ጠላትነት ለምን ተሸጋገረ?
ቅዳሜ 14 ጁን 2025 ጥዋት 4:31:37
እስራኤል በፈጸመችው ጥቃት በርካታ የአገሪቱ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዦች እና የኒውክሌር ሳይንቲስቶች መገደላቸውን ኢራን አረጋግጣለች። በጥቃቱ የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ የአየር ኃይል አዛዥን ጨምሮ ቢያንስ 20 የኢራን ወታደራዊ ኃይል ከፍተኛ አዛዦች ተገድለዋል። ይህ ኢራን የምትመካበት ወታደራዊ ኃይል ማን ነው? ምንስ አቅም አለው?
ረቡዕ 18 ጁን 2025 ጥዋት 4:08:22
በእስራኤል እና በኢራን መካከል በሚካሄደው የሚሳዔል ጥቃት ምክንያት ኢራን የዓለም ወሳኙ የነዳጅ ዘይት መተላለፊያ የሆነውን የሆሙዝ የባሕር ሰርጥን ትዘጋ ይሆናል የሚል ስጋት ቀስቅሷል። የምድራችን አንድ አምስተኛው ድፍድፍ ነዳጅ ዘይት በዚህ 40 ኪሎ ሜትር ብቻ ስፋት ባለው፣ በጣም ጠባብ በሆነው ሰርጥ በኩል ነው የሚያልፈው። እንደ የኢራን የባሕር ኃይል አዛዥ ከሆነ የባሕር ሰርጡን ለመዝጋት ልታስብ ትችላለች።
ሰኞ 18 ኦገስት 2025 ጥዋት 3:40:45
የምንመገበው ምግብ ውስጥ ሥጋ እና የእንስሳትን ተዋጽዖዎችን በምን ያህል መጠን ማካተት ይገባናል የሚለው አከራካሪ ጉዳይ ሆኖ ቀጥሏል። በኢትዮጵያውያን ዘንድ የፆም ምግብ የሚባለው ከሥጋ እና ከእንስሳት ተዋጽዖዎች ውጪ የሆነው (ቬጋን) አመጋገብ አንዳንዶች ሁሉም ሊከተሉት የሚገባ የኑሮ ዘዬ ነው ይላሉ። ሌሎች ደግሞ ይህንን አመጋገብ በጥንቃቄ ይመለከቱታል።
ሐሙስ 14 ኦገስት 2025 ጥዋት 3:57:46
ያለብንን በሽታ በትክክል ለማወቅ በጣም ውድ እና ወደ ሰውነታችን ዘልቆ በመግባት ምን እየተካሄደ እንዳለ ለማወቅ የሚያስችሉ ዘመናዊ መሣሪያዎች እንደሚያስፈልጉ እናስባለን። በእርግጥ እነዚህ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተራቀቁ የህክምና መሣሪያዎች የሚሰጡት ጠቀሜታ አስገራሚ ነው። ሆኖም ያለንበትን የጤና ሁኔታ ለማወቅ የሚያስችሉ ብቸኛ ዘዴዎች አለመሆናቸውን ብንነግራችሁስ?
ረቡዕ 13 ኦገስት 2025 ጥዋት 3:38:02
ብዙዎቻችን የራሳችንንም ሆነ የልጆቻችንን ምሥሎች እና ቪዲዮዎችን በማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ እናጋራለን። እነዚህ በበይነ መረብ ላይ የምናስቀምጣቸው መረጃዎች አሁን አሁን ለበርካቶች ደኅንነት ስጋት ለሆነው ዲፕፌክ ግብዓት እንደሚሆን ኢትዮጵያዊው ባለሙያ ይናገራሉ።
እሑድ 10 ኦገስት 2025 ጥዋት 4:59:38
በምንመገበው፣ በምንጠጣው፣ ወይም ከምንተነፍሰው አየር ውስጥ ጥቃቅን ፕላስቲኮች በሁሉም ቦታ ይገኛሉ። ከሰውነት ፈሳሾች ከምራቅ እና ከደም እስከ አክታ እና የጡት ወተት፣ ጉበት፣ ኩላሊት፣ ጣፊያ፣ አንጎል እና አጥንታችን ውስጥ ይገኛሉ። እነዚህ ሁሉ ማስረጃዎች አንድ ጥያቄን ያጭራሉ፤ ይህ ሁሉ ፕላስቲክ በጤናችን ላይ ምን እያደረገ ነው?
ሰኞ 4 ኦገስት 2025 ጥዋት 3:43:40
ማር ተፈጥሯዊ ማጣፈጫ ነው። ባክቴሪያዎች ደግሞ ጣፋጭ ነገር ይወዳሉ። ማር ግን ብልሽትን ተቋቁሞ ለረዥም ጊዜ ይቆያል። ማር ባክቴሪያዎችን ተቋቁሞ ለረዥም ጊዜ የመቆየት ምሥጢሩ ምንድን ነው?
ሰኞ 4 ኦገስት 2025 ጥዋት 3:42:17
የአፕል ዋና ሥራ አስፈጻሚ የነበረው ስቲቭ ጆብስ የሚመራው ኩባንያ አይፓድን ለገበያ ባቀረበበት ወቅት ልጆቹ ይህ ቴክኖሎጂ እንዲኖራቸው አልፈቀደም ነበር። ቢል ጌትስ፤ ልጆቹ ለቴክኖሎጂ ያላቸውን ቅርበት እንደገደበ ተናግሯል።
ሐሙስ 31 ጁላይ 2025 ጥዋት 3:58:51
ምንም እንኳ ረዥም ዓመት በጉዳዩ ላይ ጥናት እና ምርምር ቢካሄድም የዚህ መንስዔ ይህ ነው ብሎ ማመልከት አልተቻለም። የሕክምና ባለሙያዎች በወሊድ ወቅት በድንገት የሚከሰት የሆርሞን ለውጥ ሊሆን ይችላል ሲሉ ግምታቸውን ያስቀምጣሉ።
ማክሰኞ 22 ጁላይ 2025 ጥዋት 4:02:50
አንዳንድ ሰዎች እግራቸውን በየዕለቱ በአግባቡ ይታጠባሉ፤ ሌሎች ደግሞ ውሃ አፍስሰውባቸው ይተዋቸዋል። ለቅለቅ አድርገው የሚተዋቸውም ቀላል ቁጥር የላቸውም። ለመሆኑ እግሮችዎን በአግባቡ መታጣብ መጥፎ ሽታን ከማስወገድ ባሻገር እራስዎን ከበድ ካሉ የጤና ጠንቆች እየተከላከሉ መሆንዎን ያውቃሉ?
ረቡዕ 4 ጁን 2025 ጥዋት 4:00:19
ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ውስጥ በሕዝብ እና በጭነት ተሽከርካሪዎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች እና እገታዎች ተበራክተዋል። ይህ ክስተት ደግሞ ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት ላይ በሚገኘው የሰሜን ሸዋ አካባቢ በተደጋጋሚ ሲከሰት ቆይቷል። በተለይ አሊ ዶሮ የሚባለው ቦታ የጥቃት እና የእገታ ማዕከል ሆኗል እየተባለ ነው። ቢቢሲ በተለይ ይህ ቦታ ለምን የመንገደኞች እና የአሽከርካሪዎች ‘የሞት ቀጣና’ ሆነ? በሚል ለወራት የዘለቀ ምርመራ አድርጓል።
ሰኞ 12 ሜይ 2025 ጥዋት 4:02:02
ባለፉት ዓመታት በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች ውስጥ የሚካሄዱ ግጭቶች እና በታጣቂዎች የሚፈጸሙ እገታዎች ዜጎች በፈለጉት ጊዜ እና መንገድ በአገሪቱ ውስጥ እንዳይንቀሳቀሱ ብርቱ ስጋት ፈጥሮባቸዋል። በተለይ ደግሞ የመንገደኞች ማጓጓዣ ተሽከርካሪዎችን በማድረግ የሚፈጸሙት ያላባሩ እገታዎች በዋነኞቹ የአገሪቱ ክልሎች ውስጥ እንቅስቃሴን አዳጋች አድርገውታል። በዚህም ሳቢያ አቅሙ ያላቸው እና የግድ የሆነባቸው ሰዎች ፊታዎችን ወደ አየር ትራንስፖርት አዙረዋል።
ረቡዕ 2 ኤፕሪል 2025 ጥዋት 4:04:10
ዛሬ፣መጋቢት 24 የኦቲዝም ግንዛቤ ማስጨበጫ ቀን ነው። ይህ ዕለት በዓለም ደረጃ ታስቦ እንዲውል ለተባበሩት መንግሥታት ሐሳብ ያቀረበችው ኳታር ናት። ወደዚያው ብናቀና ዶክተር ወንድወሰን ግርማን እናገኛለን። ኦቲስቶች መኪና እንዲያሽከረክሩ የሚያስችል ከፍተኛ ምርምር ያደረጉ ኢትዮጵያዊ ናቸው።
ዓርብ 28 ማርች 2025 ጥዋት 4:04:02
የዓለም ጤና ድርጅት የኢትዮጵያ የአየር ብክለት ልኬት ከፍተኛ መሆኑን ያሳያል። ድርጅቱ እንደሚለው 99 በመቶው የዓለም ሕዝብ የሚተነፍሰው አየር ተበክሏል። ተላላፊ ላልሆኑ በሽታዎች የሚዳርገው የአየር ብክለት በኢትዮጵያ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ቢቢሲ ያነጋገራቸው ባለሙያ ይናገራሉ። ለመሆኑ በኢትዮጵያ ዋነኛ አየር በካዮች የትኞቹ ናቸው? መፍትሔውስ ምንድን ነው?
ዓርብ 7 ማርች 2025 ጥዋት 3:50:04
ፓላንዳዊቷ ዶ/ር ኤቫን የአማርኛ ቋንቋን ከ40 ዓመት በፊት ተምራ በዲግሪ ከተመረቀች በኋላ ከሃያ ዓመታት በላይ በማስተማር በርካቶችን በአማርኛ ቋንቋ ዲግሪ አስይዛለች። የምታስተምርበት ዩኒቨርስቲ ወደ 80 ዓመታት ለሚጠጋ ጊዜ አማርኛን እያስተማረ ነው። አማርኛ ቋንቋን “ፏፏቴ ነው” የምትለው ዶ/ር ኤቫን በአገሯ በአማርኛ አስተርጓሚነት ትሠራለች። ለመሆኑ እንዴት ከአማርኛ ጋር ተዋወቀች?
ሐሙስ 19 ዲሴምበር 2024 ጥዋት 4:54:19
በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ጉልህ ስፍራ ካላቸው ፖለቲከኞች መካከል ጃዋር መሃመድ አንዱ ነው። ለዓመታት ያህል በኦሮሚያ የነበሩ ትግሎችን እንዲሁም ተቃውሞዎችን ከጀርባም ሆነ ከፊት ሆኖ በማስተባበር እና በመምራት ግንባር ቀደም ነው።የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ፓርቲ አመራሩ ጃዋር ከትውልድ አንስቶ በፖለቲካ ህይወቱ የተጓዘበትን ህይወቱ ላይ የሚያጠነጥን ‘አልጸጸትም’ የተሰኘውን መጽሐፍ ታህሳስ 10/ 2017 ዓ.ም በኬንያዋ መዲና ናይሮቢ ያስመርቃል። ጃዋር መሃመድ በአገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ፣ በቀጣይ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ስለሚኖረው ሚና፣ አገሪቱ ስላለችበት ሁኔታ ከቢቢሲ አማርኛ ጋር ቆይታ አድርጓል።
ሰኞ 30 ሴፕቴምበር 2024 ጥዋት 4:13:42
ይህ ጥናታዊ ዘገባ የዩኒቨርስቲ መምህራን ላይ ያጠነጥናል፤ ከእነርሱም ውስጥ ፒኤችዲ (ዶክትሬት) የሚማሩት ላይ ያተኩራል። መምህራኑ የበለጠ በተማሩ ቁጥር የበለጠ እየተራቡ እንደሆነ ያወሳሉ። ቢቢሲ በርከት ያሉ የፒኤችዲ ተማሪዎችን ለወራት ቃለ መጠይቅ ሲያደርግ ቆይቷል። ከጉዳዩ ስፋት የተነሳ የብዙዎቹ አስቸጋሪ የኑሮ ሁኔታ እና ታሪክን በሚወክሉ በአምስት መምህራን ተወክሎ ቀርቧል።
ሰኞ 18 ኖቬምበር 2024 ጥዋት 3:53:07
ግንቦት 2015 ዓ.ም. የተፈጸመው የፀጋ በላቸው ጠለፋ ብዙዎችን ያስቆጣ፣ መነጋገሪያም የሆነ የወንጀል ድርጊት ነበር። ፀጋ፤ ከአንድ ዓመት ከመንፈቅ በፊት ተጠልፋ ያሳለፈቻቸውን ቀናት በተመለከተ ለመጀመሪያ ጊዜ ለቢቢሲ በዝርዝር ተናግራለች። ከቢቢሲ ጋር በነበራት ዘለግ ያለ ቆይታ፤ ስለተጠለፈችበት መንገድ እና ስላሳለፈቻቸው ዘጠኝ ቀናት በዝርዝር ተርካለች። ከጠለፋው ነጻ የወጣችበት መንገድም አስቀድሞ በክልሉ መንግሥት ከተገለጸው የተለየ እንደሆነ ለመጀመሪያ ጊዜ ተናግራለች። ለምን ከኢትዮጵያ እንደተሰደደች እና ስለ ቀጣይ ዕቅዶቿም እንዲሁ አጋርታለች።
ሰኞ 17 ማርች 2025 ጥዋት 3:41:37
“የብዙ ኢትዮጵያዊ ደም ነው የወሰደው። የኢትዮጵያ ደም ነው ያለህ እንለዋለን” ይህ በሶማሊያ የኢትዮጵያ የቀድሞ አምባሳደር ወንድሙ አሳምነው ለአሁኑ የጁባላንድ ግዛት ፕሬዚዳንት ማዶቤ በቀልድ መልኩ ጣል ያደርጉላቸው ነገር ነው። ይህ በቀልድ የተለወሰ መሪር እውነታ ነው። እውነታው የሶማሊያዋን ራስ ገዝ ጁባላንድን ላለፉት 12 ዓመታት ያስተዳደረው ማዶቤ በአንድ ወቅት በኢትዮጵያ ጦር ክፉኛ ቆስሎ በአዲስ አበባ ህክምና አድርጓል።
ቅዳሜ 19 ኤፕሪል 2025 ጥዋት 4:57:24
ወታደራዊው አስተዳደር ደርግ የአገሪቱን የመሪነት መንበር ከያዘ በኋላ የዛሬ 50 ዓመት የዕድገት በኅብረት ዘመቻን አወጀ። በዚህም ከ10ኛ ክፍል እስከ ዩኒቨርስቲ ያሉ ተማሪዎች እና መምህራን በገጠሪቱ ኢትዮጵያ ተሰማርተው በማስተማር እና በልማት ሥራዎች ላይ እንዲሳተፉ አድርጎ ነበር። በዚህ ዘመቻ የተሳተፉ የዚያ ዘመን አፍላ ወጣቶች ከአምስት አሥርታት በኋላ በጋራ ተሰባስበው ያሳለፉትን ጊዜ አስታውሰዋል። ትዝታቸውንም ለቢቢሲ አጋርተዋል. . .
ቅዳሜ 3 ሜይ 2025 ጥዋት 4:55:41
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የከበሮ፣ ጽናጽል እና መቋሚያ ንድፎችን በአዕምሯዊ ንብረትነት ማስመዝገቧን ተከትሎ ጉዳዩ ሲያከራክር ሰንብቷል። ምዝገባው ሌሎች ቤተ እምነቶች እነዚህን መገልገያዎች “እንዳይጠቀሙ የመከልከል መብት ይሰጣል ወይስ አይሰጥም?” የሚለው የክርክሩ ማጠንጠኛ ሆኗል። በዚህ ጉዳይ ላይ የቤተ ክርስቲያኗ ኃላፊዎች ያላቸው አረዳድ እና የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን አቋም የተለያየ ነው።
ዓርብ 24 ሜይ 2024 ጥዋት 4:16:17
ከእንግሊዝ ታላላቅ ቡድኖች መካከል አንዱ የሆነው የአርሰናል የልብ ደጋፊ የሆኑት ወ/ሮ እቴቱ ማሞ የ65 ዓመት እናት ናቸው። ላለፉት 20 ዓመታት አርሰናልን ያለማቋረጥ ደግፈዋል። እንደብዙዎቹ የቡድኑ ደጋፊዎች ዘንድሮ አርሰናል ዋንጫ ባለማንሳቱ ቢከፉም ድጋፋቸው ግን እንደሚቀጥል ይናገራሉ። ከሁሉም ተጫዋቾች ይልቅ እሳቸው ገብረኢየሱ ለሚሉት ለጋብሬል ጀሱስ እና ለቡካዮ ሳካ የተለየ ፍቅር አላቸው።