
ዓርብ 5 ዲሴምበር 2025 ጥዋት 3:50:24
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለሁለተኛ ጊዜ ወደ ሥልጣን ከተመለሱ በኋላ በስደተኞች ላይ ያላቸው አቋም መረር ብሏል። በተለይ ሶማሊያውያን ስደተኞችን በተመለከተ ያንጸባረቁት አቋም እና የሰነዘሩት አስተያየት አነጋጋሪ ሆኗል። ይህ የፕሬዝዳንቱ ንግግር ያሳሰበው ሶማሊያውያንን ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያውያንንም ጭምር ነው። በአሜሪካ ጥገኝነት ለማግኘት ጥያቄ አቅርበው በሂደት ላይ ያሉ ኢትዮጵያውያን ሊያደርጓቸው የሚገቡ ጥንቃቄዎችን በተመለከተ በአሜሪካ ታዋቂ የሕግ ባለሙያዎች ምክር አላቸው።

ሐሙስ 4 ዲሴምበር 2025 ከሰዓት 3:07:34
በአማራ ክልል ከሚንቀሳቀሱ ታጣቂ የፋኖ ቡድኖች አንዱ የሆነው የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) ከክልሉ መንግሥት ጋር የዘላቂ ሰላም ስምምነት መፈራረሙ ተገለጸ። የሰላም ስምምነቱ እንዲፈረም በማደራደር የአፍሪካ ኅብረት እና የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ድርጅት (ኢጋድ) መሳተፋቸውም ተነግሯል።

ሐሙስ 4 ዲሴምበር 2025 ከሰዓት 5:08:47
የታጠቁ የትግራይ ኃይል አባላት “ደመወዝ ዘገየብን” በሚል ቅሬታ መቀለ የሚገኘው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ጽሕፈት ቤት ሕንጻ ላይ ከበባ መፈጸማቸውን እና ደምጺ ወያነ ቴሌቪዥን ጣቢያን ተቆጣጥረው እንደነበረ ተገለጸ። ታጣቂዎቹ ከክልሉ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር ውይይት ያደረጉ ሲሆን አመሻሽ ላይ በከተማዋ ውስጥ ከባድ ፍንዳታ ተሰምቷል።

ሐሙስ 4 ዲሴምበር 2025 ጥዋት 7:42:23
የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ “የአፍሪካ ቀንድ ሰላም” እና “ቀጣናዊ መረጋጋትን” በተመለከተ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር በስልክ መነጋገራቸውን የዋሽንግተን የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት አስታወቀ። የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ባወጣው አጭር መገለጫ፤ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ ውይይት የተደረገው ረቡዕ ኅዳር 24/2018 ዓ.ም. መሆኑን አመልክቷል።

ሐሙስ 4 ዲሴምበር 2025 ጥዋት 7:58:24
ታላቁ ሕዳሴ ግድብን በተመለከተ የግብፅ ባለሥልጣኖች በተደጋጋሚ ለውይይት የቀረበ ጥሪን “ውድቅ አድርገዋል” እንዲሁም “ቀጥተኛ በሆነም ባልሆነም መንገድ ዛቻ ማድረስ ቀጥለዋል” ስትል ኢትዮጵያ ከሰሰች። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ትናንት ኅዳር 24/2018 ዓ. ም. ከሰዓት ባወጣው መግለጫ፤ “የግብፅ መንግሥት ወደ 21ኛው ክፍለ ዘመን መሻገር አልቻለም” ሲል ወንጅሏል። ይህ መግለጫ የወጣው የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብዲላቲ፤ ግድቡን በተመለከተ ከኢትዮጵያ ጋር “ተጨማሪ ውይይት” እንደማይደረግ ለቢቢሲ መናገራቸውን ተከትሎ ነው።

ረቡዕ 3 ዲሴምበር 2025 ጥዋት 5:06:31
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሶማሊያ ስደተኞች በአሜሪካ እንደማይፈልጉ በመግለጽ ለጋዜጠኞች “ወደመጡበት መመለስ አለባቸው” አሉ። አከለውም ከአሜሪካ ከፍተኛ ወታደራዊ ድጋፍ የምታገኘውን እና ከአልሸባብ ጋር ለአስር ዓመታት በጦርነት ውስጥ የምትገኘው ሶማሊያ “ጥሩ ያልሆነችው በምክንያት ነው” ሲሉ ተናግረዋል።

ማክሰኞ 2 ዲሴምበር 2025 ጥዋት 4:02:31
ታላቁ የሕዳሴ ግድብን በተመለከተ ከኢትዮጵያ ጋር “ተጨማሪ ውይይት” እንደማይደረግ የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብዲላቲ ተናገሩ። ከቢቢሲ ፎከስ ኦን አፍሪካ ጋር ቃለ ምልልስ ያደረጉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፤ ላለፉት 13 ዓመታት የተደረጉ ውይይቶች “አንዳችም መፍትሔ” አላመጡም ብለዋል። ሚኒስትሩ የአገራቸው ጦር በሶማሊያ ስለተሰማራበት ሁኔታም ተጠይቀው ምላሽ ሰጥተዋል።

እሑድ 30 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 8:32:41
በአሜሪካ ሁለት የብሔራዊ ዘብ አባላት ረቡዕ ዕለት በዋይት ሐውስ አቅራቢያ ከአንድ አፍጋኒስታናዊ ስደተኛ በተተኮሰባቸው ጥይት ተመትተው የአንዷ ሕይወት ሲያልፍ ሌላኛው የሕክምና ክትትል እየተደረገለት ነው። ይህንን ጥቃት ተከትሎም ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ “ከሦስተኛው ዓለም” የሚመጡ ስደተኞችን “በቋሚነት እንደሚያግዱ” ተናግረዋል። ከ19 አገራት መጥተው የመኖሪያ እና የሥራ ፈቃድ ያገኙ ግለሰቦች ሰነድም ዳግም ፍተሻ እንዲደረግበት ታዟል።

ቅዳሜ 29 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 8:16:56
ኖርዌይ የኤርትራን መንግሥት የሚደግፉ ትውልደ ኤርትራውያንን ዜግነት እንደምትነጥቅ አስታወቀች። የኖርዌይ የስደተኞች አገልግሎት ተቋም እንዳለው፤ ለሁለት ዓመታት ምርመራ ካደረገ በኋላ የኤርትራን መንግሥት የሚደግፉ ኖርዌያውያን-ኤርትራውያንን ዜግነት ለመንጠቅ ወስኗል። የኖርዌይ ዜግነት የተሰጣቸው ኤርትራውያኑ ለኤርትራ መንግሥት ድጋፍ ይሰጣሉ ያለው አምስት አባላት ያሉት መርማሪ ኮሚቴ ነው።

ሐሙስ 27 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 5:54:45
ሃይሊ ጉቢ እሳተ ገሞራ የፈነዳው ከ12ሺህ ዓመታት በኋላ ነው። እስከባለፈው እሑድ ድረስ አንዳችም እንቅስቃሴ ሳያሳይ ቆይቷል። የእሳተ ገሞራው አመድ በነፋስ አማካይነት አንድ ሺህ ጫማ ተጉዞ ጥቃቅን ቅንጣቶች ሰማይ ላይ ታይተዋል። ለመሆኑ ንቁ እሳተ ገሞራ እና ለዘብተኛ እሳተ ገሞራን ምን ይለያቸዋል? እሳተ ገሞራ ሊፈነዳ ሲል የሚያሳያቸው ምልክቶችስ የትኞቹ ናቸው?

ዓርብ 28 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 5:18:23
የትራምፕ አስተዳደር ኤርትራን ጨምሮ ከ19 አገራት ወደ አሜሪካ የገቡ በሁሉም ዜጎች የመኖሪያ እና የሥራ ፈቃድ ላይ እንደገና ምርመራ ሊያደርግ ነው።የዩናይትድ ስቴትስ የዜግነት እና የኢሚግሬሽን አገልግሎት ኃላፊ ጆሴፍ ኤድሎው እንዳሉት ፕሬዝዳንት ትራምፕ “አሳሳቢ ከሆኑ አገራት የመጡ ስደተኞች በሙሉ የእያንዳንዳቸው የመኖሪያ እና የሥራ ፈቃድ፣ በጥብቅ እንደገና እንዲመረምር” መመሪያ ሰጥተዋል።

ዓርብ 28 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 8:19:08
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ “ከሁሉም የሦስተኛው ዓለም አገራት” ስደተኞች ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ የሚያደርግ “ዘላቂ ዕገዳ” ለመጣል ዕቅድ አዳላቸው በማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ አስታወቁ። ትርምፕ ይህንን ዕቅዳቸውን ያስታወቁት በአሜሪካውያን ዘንድ የሚከበረውን “የምስጋና ቀን” በዓልን ምክንያት በማድረግ ባሰፈሩት መልዕክት ላይ ነው።

ሐሙስ 27 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 4:07:47
ምሥራቅ አፍሪካዊቷ አገር ኡጋንዳ የአፍሪካ ቀንድ አገራት ከሆኑት ከኢትዮጵያ፣ ከኤርትራ እና ከሶማሊያ ለሚመጡ ሰዎች የስደተኝነት ምዝገባ ማቆሟን አስታወቀች። ይህ ውሳኔ የተሰማው ወደ ኡጋንዳ የሚገቡ ስደተኞች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ በጨመረበት እና ከለጋሾች ለስደተኞች ተብሎ የሚመጣው ድጋፍ በመቀነሱ እንደሆነ ተዘግቧል።

ረቡዕ 19 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 4:01:04
ከሁለት ዓመት በላይ የሆነው በአማራ ክልል በመንግሥት ኃይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል በሚካሄደው ግጭት ሰላማዊ ሰዎች ከባድ ዋጋ እየከፈሉ ነው። ግጭቱ በሰው ሕይወት እና በንብረት ላይ ከሚያደርሰው ጉዳት ባሻገር በሴቶች ላይ የሚፈጸመው ጥቃት እና ሰቆቃ ትኩረትን አላገኘም። ቢቢሲ ለወራት ባካሄደው ክትትል ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሴቶች የመደፈር እና የወሲባዊ ጥቃት ሰለባ መሆናቸውን መረጃ አግኝቷል።

ሰኞ 24 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 8:40:27
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሸኔ ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት ሕጻናትና ነፍሰ ጡር እናቶችን ጨምሮ ከ40 በላይ ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች እና የአካባቢው ባለሥልጣናት ለቢቢሲ ተናገሩ። ታጣቂዎቹ ጥቃቱን በምዕራብ ኢትዮጵያ በምትገኘው ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ ቡለን ወረዳ፣ በኩጂ ቀበሌ ውስጥ የተፈጸመው ቅዳሜ ኅዳር 13/2018 ዓ.ም. ነው።

ሰኞ 24 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 4:02:28
በኢትዮጵያ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚያልፉ ተማሪዎች ከመመረቃቸው በፊት በተለያዩ መስኮች ላይ የሚሰማሩበት አሠራር ሲታሰብ ቆይቷል። ከሳምንት በፊት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ አገልግሎት በመጪው ዓመት ተግባራዊ መሆን እንደሚጀምር ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ ከተናገሩ በኋላ መነጋገሪያ ሆኗል። ይህ አገልግሎት ከ50 ዓመታት በፊት የነበረ ሲሆን ተቋርጦ ቆይቶ አሁን ዳግም ለማስጀመር ታስቧል። በዚህ ዕቅድ ዙሪያ የተለያዩ ሃሳቦች እየተሰነዘሩ ሲሆን፣ ይህ ዘገባ ታሪካዊ ዳራውን እና ተያያዥ ጉዳዮችን ይዳስሳል።

ሰኞ 17 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 4:03:52
እንዲኖረን የምንፈልገው ዓይነት ጓደኛ ለመሆን ማሻሻል ያለብን ባህሪዎች የትኞቹ ናቸው? እንዴትስ መጎ ጓደኛ መሆን ይቻላል? እነዚህ የብዙዎች ጥያቄ ናቸው።አንደኛው ጥሩ ጓደኛ መሆን የሚቻልበት መንገድ ተቃራኒ ማንነትን ማስወገድ ነው። ቋሚ መሆንን ጨምሮ በጎ ወዳጅ መሆን የሚቻልባቸውን መንገዶች እንመልከት።

ማክሰኞ 4 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 7:59:36
ሞሐመድ ሐምዳን ዳጎሎ ወይም “ሄሜቲ” ከሚመሩት የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ጋር በመሆን በአገሪቱ ፖለቲካ ውስጥ ተጽዕኖ ፈጣሪ ሆኑ እና አሁን የአገሪቱን ግማሽ የሚቆጣጠሩ ግለሰብ ናቸው። የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ የአገሪቱ ጦር እና አጋሮቹ በምዕራብ ዳርፉር የምትገኘውን የጦሩ መቀመጫ የኤል ፋሸር ከተማን በእጁ ሲያስገባ አስደናቂ ድል አግኝቷል።

ሰኞ 20 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 4:03:57
የአመጋገብ ለውጥ በማድረግ እና ከመደበኛው ሕክምና ውጪ ያሉ አማራጭ ሕክምናዎችን በመጠቀም ከካንሰር ማገገማቸውን የሚናገሩ አሉ። ለዚህም የተለያዩ ዓይነት ምግቦች፣ ቅመማ ቅመሞች እና እንቅስቃሴዎች በዓለም ዙሪያ ካንሰርን ይከላከላኑ እንዲሁም ይፈውሳሉ በሚል ጥቅም ላይ በስፋት እየዋሉ ነው። በማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይም እየተጋሩ መነጋገሪያ ከሆኑ ሰንበትበር ብለዋል። ባለሙያዎች ምን ይላሉ? እውን ለሕመሙ መፍትሄ ይሰጣሉ?

ሐሙስ 30 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 6:02:59
ሁለት አውስትራሊያውያን ወታደሮች የጻፏቸው ደብዳቤዎች ከ109 ዓመታት በኋላ ተገኙ። ጠርሙስ ውስጥ የተገኙት ደብዳቤዎች የተጻፉት በመጀመሪያው የዓለም ጦርነት ወቅት ነበር። ደብዳቤዎቹ የተገኙት በአውስትራሊያ ደቡብ ምዕራብ ባሕር ዳርቻ ነው። ሁለቱ ወታደሮች ጦርነቱን ከመቀላቀላቸው ከቀናት በፊት ደብዳቤ ጽፈው ጠርሙስ ውስጥ አኑረዋል።

ቅዳሜ 25 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 7:50:17
በሰውነት ቆዳ፣ በፀጉር እና በዐይን ሜላኒን ሳይኖር ሲቀር የሚከሰተው አልባይኒዝም (albinism) ያለባቸው ታንዛኒያውያን አገር አቀፍ ምርጫን የሚፈሩት ያለ ምክንያት አይደለም። “በተለይ በምርጫ ወቅት አልባይኖዎች ጥቃት ይደርስብናል። ከአልባይኒዝም ጋር በተያያዘ ብዙ የጥንቆላ ዕሳቤዎች አሉ። በጣም ስለምፈራ በምርጫ ቅስቀሳ አልሳተፍም” ትላለች ሜሪያም።

ማክሰኞ 14 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 3:57:07
በመካከለኛው ምሥራቅ ኃያል እና ብቸኛዋ የአይሁዶች አገር የሆነችው እስራኤል በዙሪያዋ ካሉ አገራት ሁሉ በዕድሜ ትንሿ ናት። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ማብቃት በኋላ በአውሮፓውያኑ 1948 የእስራኤል እንደ አገር መመሥረት በአካባቢው አሁን ድረስ እየተካሄደ ያለ ለውጥን አስከትሏል። ለመሆኑ በየዕለቱ የዓለም መገናኛ ብዙኃን ስሟን ሳያነሱ የማያልፏት ይህች አገር እንዴት ተመሠረተች?

ቅዳሜ 13 ሴፕቴምበር 2025 ጥዋት 4:56:17
በኳታር ዋና ከተማ ዶሃ ውስጥ እስራኤል ጥቃት የፈጸመችው በርካታ የሐማስ ፖለቲካ ቢሮ ባለሥልጣናት በሚኖሩበት የመኖሪያ አካባቢ ላይ ነው። በዚህ ጥቃት አስከ ስምንት የሚደርሱ ፍንዳታዎችን እና ከፍተኛ ጭስ በዶሃ ሰሜናዊ ክፍል ላይ ማየታቸውን ዓይን እማኞች ተናግረዋል። ከጥቃቱ ደቂቃዎች በኋላ ደግሞ እስራኤል ለተፈጸመው ጥቃት በይፋ ኃላፊነቱን ወስዳለች።

ረቡዕ 20 ኦገስት 2025 ጥዋት 3:56:27
የጠቅላይ ሚኒስትር ዴቪድ ቤን ጉርዮን መንግሥት በዓለም ታዋቂ የሆነው ሳይንቲስት አልበርት አንስታይን ለእስራኤል ፕሬዝዳንትነት እንዲሆን ካጩት በኋላ በዩናይትድ ስቴትስ የእስራኤል አምባሳደር አባ ኢባን አንስታይንን እንዲያነጋግሩ ተደረገ።

ሰኞ 11 ኦገስት 2025 ጥዋት 4:01:11
ሁለት ዓመት ሊሞላው በተቃረበው ጦርነት በጋዛ ሰርጥ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ሲገደሉ የግዛቲቱ አብዛኛው ክፍል ፈራርሷል። እስራኤል ዘመቻዋን ስትጀምር ያስቀመጠቻቸው ታጋቾችን የማስለቀቅ እና ሐማስን የመደምሰስ ዕቅዷ ከግቡ አልደረሰም። ከወዳጆቿ ሳይቀር ተቃውሞ ቢገጥማትም አሁን ደግሞ ጋዛን ሙሉ ለሙሉ የመቆጣጠር ዕቅድ እንዳላት ይፋ አድርጋለች። በርካታ መሪዎቹ የተገደሉበት ሐማስ ከዚህ ጦርነት በኋላ ዕጣ ፈንታው ምን ሊሆን ይችላል?

ሰኞ 28 ጁላይ 2025 ጥዋት 7:47:12
ማሱድ ፔዜሽኪያን ሐምሌ 2024 የኢራን ፕሬዝዳንት ሆነው ከተሾሙ ከአንድ ቀን በኋላ በቀጥታ ወደ ፖለቲካ እሳት ውስጥ ገብተዋል። ይህም አለመረጋጋት በሌለው በኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ መሪዎች ታሪክ ውስጥ ከታዩት ጅማሪዎች መካከል እጅግ አስደንጋጩ እና በቀውስ የታጀበ ነበር።

ማክሰኞ 1 ጁላይ 2025 ጥዋት 3:57:49
በአውሮፓውያኑ መጋቢት 5/1957 ዩናይትድ ስቴትስ በወቅቱ በመሐመድ ሬዛ ፓህላቪ ከምትመራው ኢራን ጋር ለሲቪል የአውቶሚክ ኢነርጂ አጠቃቀም የትብብር ስምምነት ተፈራረመች። በ’አተምስ ፎር ፒስ’ መርሃ ግብር ጥላ ስር የነበረው ይህ ስምምነት የኢራንን የኒውክሌር መርሃ ግብር ለመጀመር መሠረት ጣለ። ለዋሽንግተን፣ በዚያ የቀዝቃዛ ጦርነት ወቅት ኢራን ተጨማሪ መስህብ ነበራት።

ሐሙስ 19 ጁን 2025 ጥዋት 3:52:56
እስራኤል ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ለአርብ አጥቢያ በፈጸመችው ጥቃት ቁልፍ የሚባሉ የኢራን የጦር አዛዦች እንዲሁም የኒውክሌር ሳይንቲስቶች መገደላቸው ያሉበትን ትክክለኛ ቦታ በተመለከተ መረጃ እንዳላት የሚያሳይ ነው። ከዚህ መረጃ እና ተልዕኮ ጀርባ ደግሞ የአገሪቱ የሥለላ ተቋም ሞሳድ እንዳለ ይታመናል። ሞሳድ ባለፉት ሰባት አስርት ዓመታት ውስጥ ከኢትዮጵያ እስከ ኢራን የፈጸማቸው ዋናዎቹ ተልዕኮዎች የትኞቹ ናቸው?

ሰኞ 23 ጁን 2025 ጥዋት 3:54:51
…የኢራን ከፍተኛ ጄነራሎች እሰራኤል ጥቃት ልትሰነዝር ትችላለች የሚለው ነገር አሳስቧቸው ስብሰባ ጠሩ። ሁልጊዜም እንደሚያደርጉት ‘የእስራኤል ነገር አይታወቅም’ ብለው ከመሬት ሥር በተዘጋጀ የምድር ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ ገቡ። ሞሳድ ግን ይህን ያውቅ ነበር። ቁልፍ ስብሰባዎች እዚህ ምድር ቤት እንደሚደረጉ መረጃ ነበረው።. . .

ዓርብ 13 ጁን 2025 ጥዋት 3:51:33
ኢራን እና እስራኤል ለረጅም ጊዜ በእጅ አዙር እንጂ በቀጥታ ግጭት ውስጥ ገብተው አየውቁም። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን አንደኛው በሌላኛው ላይ የቀጥታ ጥቃት እየፈጸሙ ከጦርነት አፋፍ ላይ መድረሳቸው አሳሳቢ ሆኗል። ለመሆኑ እስራኤል እና ኢራን ጦርነት ውስጥ ቢገቡ ምን ሊከሰት ይችላል? ሁለቱ አገራትስ በወታደራዊ አቅም ምን ያህል ይመጣጠናሉ?

እሑድ 15 ጁን 2025 ጥዋት 4:51:06
ኢራን ከግብፅ ቀጥላ ለእስራኤል እውቅና በመስጠት ሁለተኛዋ እስላማዊ አገር ነበረች። ነገር ግን ከኢራን እስላማዊ አብዮት በኋላ ይህ ግንኙነት ተበላሽቶ ከአራት አስርታት በላይ በጠላትነት እየተያዩ ቆይተዋል። ለመሆኑ የሁለቱ አገራት ግንኙነት ወደ ደመኛ ጠላትነት ለምን ተሸጋገረ?

ቅዳሜ 14 ጁን 2025 ጥዋት 4:31:37
እስራኤል በፈጸመችው ጥቃት በርካታ የአገሪቱ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዦች እና የኒውክሌር ሳይንቲስቶች መገደላቸውን ኢራን አረጋግጣለች። በጥቃቱ የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ የአየር ኃይል አዛዥን ጨምሮ ቢያንስ 20 የኢራን ወታደራዊ ኃይል ከፍተኛ አዛዦች ተገድለዋል። ይህ ኢራን የምትመካበት ወታደራዊ ኃይል ማን ነው? ምንስ አቅም አለው?

ሰኞ 17 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 4:03:52
እንዲኖረን የምንፈልገው ዓይነት ጓደኛ ለመሆን ማሻሻል ያለብን ባህሪዎች የትኞቹ ናቸው? እንዴትስ መጎ ጓደኛ መሆን ይቻላል? እነዚህ የብዙዎች ጥያቄ ናቸው።አንደኛው ጥሩ ጓደኛ መሆን የሚቻልበት መንገድ ተቃራኒ ማንነትን ማስወገድ ነው። ቋሚ መሆንን ጨምሮ በጎ ወዳጅ መሆን የሚቻልባቸውን መንገዶች እንመልከት።

ዓርብ 14 ኖቬምበር 2025 ከሰዓት 3:38:17
በደቡብ ኢትዮጵያ በጂንካ ከተማ ተከስቶ ለስድስት ሰዎች ሞት ምክንያት የሆነው በሽታ ማርበርግ ቫይረስ መሆኑን የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር አስታወቀ። ከኢትዮጵያ በስተደቡብ በሚገኙ አገራት ውስጥ ተከስቶ የነበረው ይህ በሽታ ከሳምንት በፊት ነው በደቡብ ኢትዮጵያ አካባቢዎች ተከስቶ ሁለት የጤና ባለሙያዎችን ጨምሮ ስድስት ሰዎችን የገደለው።

ሐሙስ 13 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 4:03:08
ሰውነታችንን አሊያም እጃችንን የምንደርቅባቸው ፎጣዎች ብዙ ጠቀሜታ ቢሰጡም እግረ መንገዳቸውን ረቂቅ ተህዋስያንን ከሰውነታችን ላይ ያነሳሉ።ፎጣዎቻችን ለምን ዓይነት በሽታዎች ያጋልጡናል? ፎጣዎችን ሳናጥብ ለምን ያህል ጊዜ እንጠቀምባቸዋለን? በምን ያህል ጊዜስ መታጠብ አለባቸወ?

እሑድ 9 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 4:58:10
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የእድሳት ሥራው የተጠናቀቀውን የፋሲል ግንብ መርቀዋል። ባለፈው ዓመት የጥገና እድሳት እየተከናወለት በነበረበት ወቅት የግንቡ ታሪካዊ ሽሯሟ ቀለም ነጥቶ መታየቱ በርካታ መላምት እንዲሰጥ አድርጎ ነበር። የታሪካዊው ግንብ ቀለም ለዘመናት ከሚታወቅበት ተለውጦ ለምን ነጣ? የሚል ጥያቄ እንዲነሳም ምክንያት ሆኗል።በጥገና እድሳቱ በአማካሪነት እንዲሁም በጥናት የተሳተፉት አንጋፋው አርክቴክት ፋሲል ጊዮርጊስ በወቅቱ ከቢቢሲ ጋር ቆይታ በማድረግ ለጉዳዩ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ቅዳሜ 1 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 4:53:34
ሰሞኑን አረቄ ብሔራዊ አጀንዳ ሆና የማኅበራዊ ሚዲያ አናት ላይ ወጥታ ነበር። ጠጅ ቢሆን አናት ላይ አይወጣም፤ ወደ ጉልበት ነው የሚወርደው። ጠጅ ለመጨረሻ ጊዜ ጉዳይ ሆኖ የሥነ መንግሥቱ አናት ላይ ወጥቶ፣ ‘ብሔራዊ አጀንዳ’ የነበረው በዐፄ ዮሐንስ 4ኛ ዘመን ነው። ድሮ ጠጅ በብርሌ ይቀርብ ነበር። ከዚያ በብርሌ ይጠጣ ጀመር። ጠጅ ግን እንደ አረቄ ማንም ‘ተራ ዜጋ’ ብድግ አድርጎ አያንደቀድቀውም።ብርሌ ውስጥ የመደብ ታሪክ አለ። የዘመን ታሪክ አለ። የጭሰኛና የመሳፍንት ታሪክ አለ። ያልተሳከረ።

ቅዳሜ 22 ፌብሩዋሪ 2025 ጥዋት 4:53:16
ከተከፈተ በዚህ ወር 20 ዓመት የሆነው የቪዲዮ ማጋሪያው የማኅበራዊ ሚዲያ መድረክ ዩቲዩብ ለብዙዎች የተለያዩ አጋጣሚዎችን ፈጥሯል። ከእነዚህም መካከል አቤል ብርሃኑ አንዱ ነው፤ በዩቲዩብ አማካኝነት 62 ሀገራትን ዟሯል። ያልረገጠው አህጉር አንታርቲካን ብቻ ነው። ሁሉንም የአሜሪካ ግዛቶች አካሏል። ከዘጠኝ ዓመታት በላይ ዩቲዩብ ላይ የቆየው አቤል ከዩቲዩብ ምንያህል ያገኛል?

ዓርብ 24 ሜይ 2024 ጥዋት 4:16:17
ከእንግሊዝ ታላላቅ ቡድኖች መካከል አንዱ የሆነው የአርሰናል የልብ ደጋፊ የሆኑት ወ/ሮ እቴቱ ማሞ የ65 ዓመት እናት ናቸው። ላለፉት 20 ዓመታት አርሰናልን ያለማቋረጥ ደግፈዋል። እንደብዙዎቹ የቡድኑ ደጋፊዎች ዘንድሮ አርሰናል ዋንጫ ባለማንሳቱ ቢከፉም ድጋፋቸው ግን እንደሚቀጥል ይናገራሉ። ከሁሉም ተጫዋቾች ይልቅ እሳቸው ገብረኢየሱ ለሚሉት ለጋብሬል ጀሱስ እና ለቡካዮ ሳካ የተለየ ፍቅር አላቸው።

ረቡዕ 4 ጁን 2025 ጥዋት 4:00:19
ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ውስጥ በሕዝብ እና በጭነት ተሽከርካሪዎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች እና እገታዎች ተበራክተዋል። ይህ ክስተት ደግሞ ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት ላይ በሚገኘው የሰሜን ሸዋ አካባቢ በተደጋጋሚ ሲከሰት ቆይቷል። በተለይ አሊ ዶሮ የሚባለው ቦታ የጥቃት እና የእገታ ማዕከል ሆኗል እየተባለ ነው። ቢቢሲ በተለይ ይህ ቦታ ለምን የመንገደኞች እና የአሽከርካሪዎች ‘የሞት ቀጣና’ ሆነ? በሚል ለወራት የዘለቀ ምርመራ አድርጓል።

ሰኞ 18 ኖቬምበር 2024 ጥዋት 3:53:07
ግንቦት 2015 ዓ.ም. የተፈጸመው የፀጋ በላቸው ጠለፋ ብዙዎችን ያስቆጣ፣ መነጋገሪያም የሆነ የወንጀል ድርጊት ነበር። ፀጋ፤ ከአንድ ዓመት ከመንፈቅ በፊት ተጠልፋ ያሳለፈቻቸውን ቀናት በተመለከተ ለመጀመሪያ ጊዜ ለቢቢሲ በዝርዝር ተናግራለች። ከቢቢሲ ጋር በነበራት ዘለግ ያለ ቆይታ፤ ስለተጠለፈችበት መንገድ እና ስላሳለፈቻቸው ዘጠኝ ቀናት በዝርዝር ተርካለች። ከጠለፋው ነጻ የወጣችበት መንገድም አስቀድሞ በክልሉ መንግሥት ከተገለጸው የተለየ እንደሆነ ለመጀመሪያ ጊዜ ተናግራለች። ለምን ከኢትዮጵያ እንደተሰደደች እና ስለ ቀጣይ ዕቅዶቿም እንዲሁ አጋርታለች።

ሰኞ 12 ሜይ 2025 ጥዋት 4:02:02
ባለፉት ዓመታት በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች ውስጥ የሚካሄዱ ግጭቶች እና በታጣቂዎች የሚፈጸሙ እገታዎች ዜጎች በፈለጉት ጊዜ እና መንገድ በአገሪቱ ውስጥ እንዳይንቀሳቀሱ ብርቱ ስጋት ፈጥሮባቸዋል። በተለይ ደግሞ የመንገደኞች ማጓጓዣ ተሽከርካሪዎችን በማድረግ የሚፈጸሙት ያላባሩ እገታዎች በዋነኞቹ የአገሪቱ ክልሎች ውስጥ እንቅስቃሴን አዳጋች አድርገውታል። በዚህም ሳቢያ አቅሙ ያላቸው እና የግድ የሆነባቸው ሰዎች ፊታዎችን ወደ አየር ትራንስፖርት አዙረዋል።

ረቡዕ 2 ኤፕሪል 2025 ጥዋት 4:04:10
ዛሬ፣መጋቢት 24 የኦቲዝም ግንዛቤ ማስጨበጫ ቀን ነው። ይህ ዕለት በዓለም ደረጃ ታስቦ እንዲውል ለተባበሩት መንግሥታት ሐሳብ ያቀረበችው ኳታር ናት። ወደዚያው ብናቀና ዶክተር ወንድወሰን ግርማን እናገኛለን። ኦቲስቶች መኪና እንዲያሽከረክሩ የሚያስችል ከፍተኛ ምርምር ያደረጉ ኢትዮጵያዊ ናቸው።

ዓርብ 28 ማርች 2025 ጥዋት 4:04:02
የዓለም ጤና ድርጅት የኢትዮጵያ የአየር ብክለት ልኬት ከፍተኛ መሆኑን ያሳያል። ድርጅቱ እንደሚለው 99 በመቶው የዓለም ሕዝብ የሚተነፍሰው አየር ተበክሏል። ተላላፊ ላልሆኑ በሽታዎች የሚዳርገው የአየር ብክለት በኢትዮጵያ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ቢቢሲ ያነጋገራቸው ባለሙያ ይናገራሉ። ለመሆኑ በኢትዮጵያ ዋነኛ አየር በካዮች የትኞቹ ናቸው? መፍትሔውስ ምንድን ነው?

ዓርብ 7 ማርች 2025 ጥዋት 3:50:04
ፓላንዳዊቷ ዶ/ር ኤቫን የአማርኛ ቋንቋን ከ40 ዓመት በፊት ተምራ በዲግሪ ከተመረቀች በኋላ ከሃያ ዓመታት በላይ በማስተማር በርካቶችን በአማርኛ ቋንቋ ዲግሪ አስይዛለች። የምታስተምርበት ዩኒቨርስቲ ወደ 80 ዓመታት ለሚጠጋ ጊዜ አማርኛን እያስተማረ ነው። አማርኛ ቋንቋን “ፏፏቴ ነው” የምትለው ዶ/ር ኤቫን በአገሯ በአማርኛ አስተርጓሚነት ትሠራለች። ለመሆኑ እንዴት ከአማርኛ ጋር ተዋወቀች?

ሐሙስ 19 ዲሴምበር 2024 ጥዋት 4:54:19
በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ጉልህ ስፍራ ካላቸው ፖለቲከኞች መካከል ጃዋር መሃመድ አንዱ ነው። ለዓመታት ያህል በኦሮሚያ የነበሩ ትግሎችን እንዲሁም ተቃውሞዎችን ከጀርባም ሆነ ከፊት ሆኖ በማስተባበር እና በመምራት ግንባር ቀደም ነው።የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ፓርቲ አመራሩ ጃዋር ከትውልድ አንስቶ በፖለቲካ ህይወቱ የተጓዘበትን ህይወቱ ላይ የሚያጠነጥን ‘አልጸጸትም’ የተሰኘውን መጽሐፍ ታህሳስ 10/ 2017 ዓ.ም በኬንያዋ መዲና ናይሮቢ ያስመርቃል። ጃዋር መሃመድ በአገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ፣ በቀጣይ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ስለሚኖረው ሚና፣ አገሪቱ ስላለችበት ሁኔታ ከቢቢሲ አማርኛ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ሰኞ 30 ሴፕቴምበር 2024 ጥዋት 4:13:42
ይህ ጥናታዊ ዘገባ የዩኒቨርስቲ መምህራን ላይ ያጠነጥናል፤ ከእነርሱም ውስጥ ፒኤችዲ (ዶክትሬት) የሚማሩት ላይ ያተኩራል። መምህራኑ የበለጠ በተማሩ ቁጥር የበለጠ እየተራቡ እንደሆነ ያወሳሉ። ቢቢሲ በርከት ያሉ የፒኤችዲ ተማሪዎችን ለወራት ቃለ መጠይቅ ሲያደርግ ቆይቷል። ከጉዳዩ ስፋት የተነሳ የብዙዎቹ አስቸጋሪ የኑሮ ሁኔታ እና ታሪክን በሚወክሉ በአምስት መምህራን ተወክሎ ቀርቧል።

ሰኞ 17 ማርች 2025 ጥዋት 3:41:37
“የብዙ ኢትዮጵያዊ ደም ነው የወሰደው። የኢትዮጵያ ደም ነው ያለህ እንለዋለን” ይህ በሶማሊያ የኢትዮጵያ የቀድሞ አምባሳደር ወንድሙ አሳምነው ለአሁኑ የጁባላንድ ግዛት ፕሬዚዳንት ማዶቤ በቀልድ መልኩ ጣል ያደርጉላቸው ነገር ነው። ይህ በቀልድ የተለወሰ መሪር እውነታ ነው። እውነታው የሶማሊያዋን ራስ ገዝ ጁባላንድን ላለፉት 12 ዓመታት ያስተዳደረው ማዶቤ በአንድ ወቅት በኢትዮጵያ ጦር ክፉኛ ቆስሎ በአዲስ አበባ ህክምና አድርጓል።

ቅዳሜ 19 ኤፕሪል 2025 ጥዋት 4:57:24
ወታደራዊው አስተዳደር ደርግ የአገሪቱን የመሪነት መንበር ከያዘ በኋላ የዛሬ 50 ዓመት የዕድገት በኅብረት ዘመቻን አወጀ። በዚህም ከ10ኛ ክፍል እስከ ዩኒቨርስቲ ያሉ ተማሪዎች እና መምህራን በገጠሪቱ ኢትዮጵያ ተሰማርተው በማስተማር እና በልማት ሥራዎች ላይ እንዲሳተፉ አድርጎ ነበር። በዚህ ዘመቻ የተሳተፉ የዚያ ዘመን አፍላ ወጣቶች ከአምስት አሥርታት በኋላ በጋራ ተሰባስበው ያሳለፉትን ጊዜ አስታውሰዋል። ትዝታቸውንም ለቢቢሲ አጋርተዋል. . .

ቅዳሜ 3 ሜይ 2025 ጥዋት 4:55:41
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የከበሮ፣ ጽናጽል እና መቋሚያ ንድፎችን በአዕምሯዊ ንብረትነት ማስመዝገቧን ተከትሎ ጉዳዩ ሲያከራክር ሰንብቷል። ምዝገባው ሌሎች ቤተ እምነቶች እነዚህን መገልገያዎች “እንዳይጠቀሙ የመከልከል መብት ይሰጣል ወይስ አይሰጥም?” የሚለው የክርክሩ ማጠንጠኛ ሆኗል። በዚህ ጉዳይ ላይ የቤተ ክርስቲያኗ ኃላፊዎች ያላቸው አረዳድ እና የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን አቋም የተለያየ ነው።