world-service-rss

BBC News አማርኛ

የኤርትራን “የግዛት አንድነት ጥሰቶች” በተመለከተ መንግሥት የያዘው “የመታቀብ” አቋም “ሁሌም እንደማይቀጥል” ዶ/ር ጌዲዮን አሳሰቡ

የኤርትራን "የግዛት አንድነት ጥሰቶች" በተመለከተ መንግሥት የያዘው "የመታቀብ" አቋም "ሁሌም እንደማይቀጥል" ዶ/ር ጌዲዮን አሳሰቡ

ዓርብ 14 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 10:45:30

ኤርትራ በኢትዮጵያ “ሉዐላዊነት እና የግዛት አንድነት” ላይ የምትፈጽማቸው “ጥሰቶችን” በተመለከተ የፌደራል መንግሥት የያዘው እርምጃ ከመውሰድ “የመታቀብ” አካሄድ “ሁሌም የሚቀጥል እና ገደብ የለሽ ተደርጎ መወሰድ እንደሌለበት” የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ተናገሩ። ዶ/ር ጌዲዮን፤ ኢትዮጵያ “ከኤርትራ መገንጠል በፊት እና በኋላ” በአሰብ ወደብ ላይ “ባፈሰሰችው ከፍተኛ ሀብት ምክንያት”፤ አሰብ በፌደራል መንግሥት “በዋነኛነት ቅድሚያ የሚሰጠው” ጉዳይ እንደሆነ መግለጻቸውም ተዘግቧል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ለሰዎች ሞት ምክንያት የሆነው ማርበርግ ቫይረስ መሆኑ ታወቀ፤ ክትባት ወይም መድኃኒት አለው?

በደቡብ ኢትዮጵያ ለሰዎች ሞት ምክንያት የሆነው ማርበርግ ቫይረስ መሆኑ ታወቀ፤ ክትባት ወይም መድኃኒት አለው?

ዓርብ 14 ኖቬምበር 2025 ከሰዓት 3:38:17

በደቡብ ኢትዮጵያ በጂንካ ከተማ ተከስቶ ለስድስት ሰዎች ሞት ምክንያት የሆነው በሽታ ማርበርግ ቫይረስ መሆኑን የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር አስታወቀ። ከኢትዮጵያ በስተደቡብ በሚገኙ አገራት ውስጥ ተከስቶ የነበረው ይህ በሽታ ከሳምንት በፊት ነው በደቡብ ኢትዮጵያ አካባቢዎች ተከስቶ ሁለት የጤና ባለሙያዎችን ጨምሮ ስድስት ሰዎችን የገደለው።

በምርጫ ለመሳተፍ በቅድመ ሁኔታ እና ሕጋዊነትን በማጣት መካከል የተወጠሩት የፖለቲካ ፓርቲዎች

በምርጫ ለመሳተፍ በቅድመ ሁኔታ እና ሕጋዊነትን በማጣት መካከል የተወጠሩት የፖለቲካ ፓርቲዎች

ዓርብ 14 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 4:09:31

አስር ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ስብስብ በዚህ ዓመት የሚካሄደው ምርጫ ነፃ፣ ፍትሃዊና ተዓማኒ እንዲሆን እና “ከአጃቢነት ያለፈ ተሳትፎ” እንዲኖራቸው የሚጠይቅ ቅድመ ሁኔታዎችን አቀረቡ። ራሳቸውን የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች አንድነት መድረክ (መድረክ) ሲሉ የሚጠሩት 10 የተቃዋሚ ፓርቲዎች ስብስብ ኅዳር 3/2018 ዓ.ም. በጋራ ባወጡት መግለጫ ላይ “ሕጋዊነትን ለመላበስ የሚደረጉ የፖለቲካ ትወናዎች” ሲሉ ከዚህ ቀደም የተደረጉ ምርጫዎችን በመኮነን፤ ምርጫዎቹ “ነፃ፣ ፍትሃዊ እና አሳታፊ፤ በውጤታቸውም ተዓማኒ እና በሕዝብ ተቀባይነት አላገኙም” ሲሉ ተችተዋል።

በጂንካ ከተማ የተከሰተውን በሽታ “ሲያክሙ የነበሩ” ሁለት የጤና ባለሙያዎችን ጨምሮ ስድስት ሰዎች ሞቱ

በጂንካ ከተማ የተከሰተውን በሽታ "ሲያክሙ የነበሩ" ሁለት የጤና ባለሙያዎችን ጨምሮ ስድስት ሰዎች ሞቱ

ሐሙስ 13 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 8:59:11

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ ጂንካ ከተማ በተከሰተው በውል ያልታወቀ በሽታ ለተያዙ ሰዎች “ሕምክና ሲሰጡ የነበሩ” ሁለት የጤና ባለሙያዎችን ጨምሮ ስድስት ሰዎች መሞታቸውን የጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታል ለቢቢሲ ገለጸ። የጤና ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በጂንካ ከተማ “ምንነቱ በመረጋገጥ ላይ ያለ የሔሞራጂክ ፊቨር” በሽታ መከሰቱን ያስታወቁት ትናንት ረቡዕ ሕዳር 3/2018 ዓ.ም. በጋራ ባወጡት መግለጫ ነው። በሽታው መከሰቱን ያመለከቱት “የቅኝት መረጃዎች” መሆናቸውን የገለጸው መግለጫው፤ ስምንት ሰዎች “በበሽታው እንደተጠረሩም” ገልጿል።

በሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ እጃቸው ያለበት የውጭ አገራት የትኞቹ ናቸው?

በሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ እጃቸው ያለበት የውጭ አገራት የትኞቹ ናቸው?

ሐሙስ 13 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 4:02:04

የሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት ከሁለት ዓመት ተኩል በኋላም ተባብሶ እንደቀጠለ ነው። ጦርነቱ እንዲራዘም ምክንያት ከሆኑ መካከል የውጭ አገራት ጣልቃ ገብነት ይጠቀሳል። ለጦርነቱ መቀጠል አስተዋጽኦ ያደረጉ ለሁለቱ ተፋላሚ ኃይሎች የፖለቲካ እና ወታደራዊ ድጋፍ የሚያደርጉ አገራት አሉ። በጦርነቱ ሳቢያ ከ150,000 በላይ ሰዎች ሲገደሉ፤ ከ12 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል።

የሚድሮኩ ሆራይዘን ፕላንቴሽንስ እንዴት “በሕጻናት ጉልበት ብዝበዛ” እና “በታፈሱ ሰዎች” ቅጥር ተጠያቂ ሳይሆን ቀረ?

የሚድሮኩ ሆራይዘን ፕላንቴሽንስ እንዴት "በሕጻናት ጉልበት ብዝበዛ" እና "በታፈሱ ሰዎች" ቅጥር ተጠያቂ ሳይሆን ቀረ?

ማክሰኞ 11 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 3:58:03

በሚድሮክ ስር የሚገኘው ሆራይዘን ፕላንቴሽንስ ሕጻናት ተማሪዎችን ቡና ለቀማ ላይ ሲያሰማራ እንደነበረ ይፋ ያልተደረገ የኢሰመኮ ሪፖርት እና ቢቢሲ ያነጋገራቸው ምንጮች አረጋገጡ። ከአዲስ አበባ ጎዳናዎች በፖሊስ የታፈሱ ነዋሪዎችም ወደ ኩባንያው እርሻዎች ሲወሰዱ እንደነበር ቢቢሲ ያደረገው ክትትል አሳይቷል። በዚህ ልዩ ዘገባ፤ ቢቢሲ የተመለከተው የኢሰመኮ ሪፖርት እና የሠራተኞች እማኝነት በዝርዝር ቀርበዋል። ባለሥልጣናት እስካሁን ድረስ ለምን የሕግ ተጠያቂነትን እንዳላሰፈኑም ተጠይቀዋል።

የፕሪቶሪያ ስምምነት ለምን ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ አልሆነም? አዲስ ስምምነትስ ያስፈልጋል?

የፕሪቶሪያ ስምምነት ለምን ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ አልሆነም? አዲስ ስምምነትስ ያስፈልጋል?

ዓርብ 7 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 4:02:54

በሁለት ዓመት ውስጥ ከፍተኛ ሰብአዊ እና ቁሳዊ ጉዳት እንዲሁም ውድመትን ያስከተለውን ደም አፋሳሹን ጦርነት ያስቆመው የፕሪቶሪያው ስምምነት ከተፈረመ ሦስት ዓመት ሆኖታል። ነገር ግን ሁሉም የስምምነቱ ነጥቦች ተግባራዊ ባለመሆናቸው ዳግም ወደ ግጭት እንዳይገባ ስጋት ተፈጥሯል። የስምምነቱ ቁልፍ ጉዳዮችን ተግባራዊ ባለማድረግ የፌደራል መንግሥቱ እና ህወሓት እየተካሰሱ ሲሆን፣ በቀጣይነትም የስምምነቱ እውን መሆን ጥያቄ ውስጥ እየገባ ነው። የፕሪቶሪያ ስምምነት ዕጣ ፈንታ ምን ሊሆን ይችላል?

የትግራይ ኃይሎች “15 ኪሎ ሜትር ዘልቀው” ወደ አፋር ክልል መጋሌ ወረዳ ገብተዋል ሲሉ ዋና አስተዳዳሪው ከሰሱ

የትግራይ ኃይሎች "15 ኪሎ ሜትር ዘልቀው" ወደ አፋር ክልል መጋሌ ወረዳ ገብተዋል ሲሉ ዋና አስተዳዳሪው ከሰሱ

ሐሙስ 6 ኖቬምበር 2025 ከሰዓት 12:23:31

የአፋር ክልል መጋሌ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ፤ የትግራይ ኃይሎች በወረዳው ቶንሳ ቀበሌ ላይ “በከፈቱት ጥቃት”፤ “ወደ 15 ኪሎ ሜትር ዘልቀው” መግባታቸውን እና “ስድስት መንደሮችን” መቆጣጠራቸውን በመግለጽ ከሰሱ። የትግራይ ክልል ሰላም እና ፀጥታ ቢሮ በበኩሉ “የከፈትነው ጥቃትም ሆነ የተቆጣጠርነው መሬት የለም” ሲል ወንጀላውን አጣጥሏል።

ህወሓት በትግራይ ኃይል አባላት ላይ የድሮን ጥቃት መፈጸሙን ገለጸ

ህወሓት በትግራይ ኃይል አባላት ላይ የድሮን ጥቃት መፈጸሙን ገለጸ

ዓርብ 7 ኖቬምበር 2025 ከሰዓት 3:56:43

ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) የኢትዮጵያ መንግሥት የድሮን ጥቃት በመፈጸም በትግራይ ኃይሎች አባላት ላይ ጉዳት ማድረሱን ገለጸ። ህወሓት አርብ ማምሻውን ባወጣው መግለጫ የትግራይ ክልል ከአፋር ክልል ጋር በሚዋሰንበት አካባቢ አርብ ጥቅምት 28/2018 ዓ.ም. በተፈጸመው የድሮን ጥቃት ዝርዝሩን ባይገልጽም ጉዳት መድረሱን አመልክቷል።

መንግሥት “በውጭ ምንዛሪ አሻጥር” የጠረጠራቸውን 112 ሰዎችን ሲይዝ ከ500 በላይ አካውንቶችን አገደ

መንግሥት "በውጭ ምንዛሪ አሻጥር" የጠረጠራቸውን 112 ሰዎችን ሲይዝ ከ500 በላይ አካውንቶችን አገደ

ሰኞ 10 ኖቬምበር 2025 ከሰዓት 4:01:24

በሕገ ወጥ የውጭ ምንዛሪ አሻጥሮችን ሲፈጽሙ ነበር የተባሉ በርካታ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን እና ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የባንክ አካውንቶች መታገዳቸውን የመንግሥት የፀጥታ እና ደኅንነት አካላት አስታወቁ። የብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አገልግሎት፣ የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት፣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ እና የክልል የፀጥታ ተቋማት በወሰዱት እርምጃ በሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር ላይ ተሳትፈዋል ተብለው የተጠረጠሩ ግለሰቦች እና አካወንቶች ናቸው ለእስር እና ለዕግድ የበቁት።

ኢትዮጵያውያን የኒው ዮርክ ነዋሪዎችን ያመሰገነው የመጀመሪያው ሙስሊም ከንቲባ ዞህራን ማምዳኒ

ኢትዮጵያውያን የኒው ዮርክ ነዋሪዎችን ያመሰገነው የመጀመሪያው ሙስሊም ከንቲባ ዞህራን ማምዳኒ

ረቡዕ 5 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 4:12:33

የ34 ዓመቱ ዞህራን ክዋሜ ማምዳኒ የኒው ዮርክ ከንቲባ ሆኖ ተመረጠ። በአሜሪካ ትልቋ ከተማ ኒው ዮርክ ለከንቲባነት በመመረጥ የመጀመሪያው ሙስሊም በመሆን ታሪክ ሠርቷል። ዞህራን የኒው ዮርክ ከንቲባ እንዲሆን ንቅናቄ ያደረጉ እና ድምጽ የሰጡ ነዋሪዎችንም በንግግሩ ሳይጠቅስ አላለፈም። “የመናውያን የመደብር ባለቤቶች፣ ሴኔጋላውያን የታክሲ ሹፌሮች፣ ኡዝቤክስታናውያን ነርሶች እና ኢትዮጵያውያን ‘አክስቶች’ “ ሲል ድጋፍ የሰጡትን ዘርዝሯል።

ኢትዮጵያን ያገለለው በግብፅ እና በሳዑዲ የሚመራው የቀይ ባሕር መድረክ ዓላማው ምንድን ነው?

ኢትዮጵያን ያገለለው በግብፅ እና በሳዑዲ የሚመራው የቀይ ባሕር መድረክ ዓላማው ምንድን ነው?

ሰኞ 3 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 3:59:23

በሕዳሴው ግድብ ምክንያት ከኢትዮጵያ ጋር ውዝግብ ውስጥ የገባችው ግብፅ፣ ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር ጉዳይ ውስጥ የሚያገባት ነገር የለም ብላለች። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯ ባለፈው ሳምንት እንደተናገሩት “በተለይ ኢትዮጵያ” በማለት የባሕር በር የሌላቸው አገራት የቀይ ባሕር አስተዳደር ጉዳይ አይመለከታቸውም የለም ብለዋል። ኢትዮጵያ የተገለለችበትን የቀይ ባሕር ትብብር መድረክን የምትመራው ግብፅ በቀጣናው ያላት ተፅእኖ ምን ያህል ነው? የቀይ ባሕር ትብብር መድረክ አባላት እነ ማን ናቸው? ዓላማውስ ምንድን ነው?

ግመሎችን እና ወርቅ በመሸጥ ሃብት ያካበቱት፣ አሁን ደግሞ ከፊል ሱዳንን የሚቆጣጠሩት ሐምዳን ዳጎሎ

ግመሎችን እና ወርቅ በመሸጥ ሃብት ያካበቱት፣ አሁን ደግሞ ከፊል ሱዳንን የሚቆጣጠሩት ሐምዳን ዳጎሎ

ማክሰኞ 4 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 7:59:36

ሞሐመድ ሐምዳን ዳጎሎ ወይም “ሄሜቲ” ከሚመሩት የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ጋር በመሆን በአገሪቱ ፖለቲካ ውስጥ ተጽዕኖ ፈጣሪ ሆኑ እና አሁን የአገሪቱን ግማሽ የሚቆጣጠሩ ግለሰብ ናቸው። የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ የአገሪቱ ጦር እና አጋሮቹ በምዕራብ ዳርፉር የምትገኘውን የጦሩ መቀመጫ የኤል ፋሸር ከተማን በእጁ ሲያስገባ አስደናቂ ድል አግኝቷል።

“ሕልም ስላለኝ ብታመምም መኖር፣ መታገል እና ታትሮ መሥራትን አላቋርጥም”- በካንሰር የታመሙት ሌሊሴ ዱጋ

"ሕልም ስላለኝ ብታመምም መኖር፣ መታገል እና ታትሮ መሥራትን አላቋርጥም"- በካንሰር የታመሙት ሌሊሴ ዱጋ

ረቡዕ 5 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 10:24:14

የኦሮሚያ የቱሪዝም ኮሚሽን ኮሚሽነር ሌሊሴ ዱጋ የካንሰር ሕክምና እየተከታተሉ መሆናቸውን በመግለጽ ፎቷቸውን ጭምር አያይዘው በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ከቀናት በፊት አጋርተው ነበር። ቢቢሲም ሌሊሴን ሕክምና እየተከታተሉ ከሚገኙበት የመካከለኛው ምሥራቋ ዮርዳኖስ በስልክ አግኝቷቸው ስላሉበት ሁኔታ አጭር ቆይታ አድርጓል።

በብርሌ ፍቅር የወደቁት ፈረንጅ ‘ብርሌ ውስጥ የኢትዮጵያ ታሪክ አለ’ ይላሉ

በብርሌ ፍቅር የወደቁት ፈረንጅ 'ብርሌ ውስጥ የኢትዮጵያ ታሪክ አለ' ይላሉ

ቅዳሜ 1 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 4:53:34

ሰሞኑን አረቄ ብሔራዊ አጀንዳ ሆና የማኅበራዊ ሚዲያ አናት ላይ ወጥታ ነበር። ጠጅ ቢሆን አናት ላይ አይወጣም፤ ወደ ጉልበት ነው የሚወርደው። ጠጅ ለመጨረሻ ጊዜ ጉዳይ ሆኖ የሥነ መንግሥቱ አናት ላይ ወጥቶ፣ ‘ብሔራዊ አጀንዳ’ የነበረው በዐፄ ዮሐንስ 4ኛ ዘመን ነው። ድሮ ጠጅ በብርሌ ይቀርብ ነበር። ከዚያ በብርሌ ይጠጣ ጀመር። ጠጅ ግን እንደ አረቄ ማንም ‘ተራ ዜጋ’ ብድግ አድርጎ አያንደቀድቀውም።ብርሌ ውስጥ የመደብ ታሪክ አለ። የዘመን ታሪክ አለ። የጭሰኛና የመሳፍንት ታሪክ አለ። ያልተሳከረ።

“ሰይጣን አምላኪዎች ልጄን በማኅበራዊ ሚዲያ አጠመዷት፤ እንዳላድናት አቅመቢስ ሆንኩ”

"ሰይጣን አምላኪዎች ልጄን በማኅበራዊ ሚዲያ አጠመዷት፤ እንዳላድናት አቅመቢስ ሆንኩ"

ረቡዕ 29 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 3:51:14

የ14 ዓመቷ ታዳጊ ከዕድሜ እኩዮቿ ጋር በበይነ መረብ ስታወራ እናቷ እምብዛም አላሳሰባትም ነበር። ከሳምንታት በኋላ ግን የታዳጊዋ ባህሪ ተለወጠ። ለዚህ ጽሑፍ ስንል ክርስቲና የምንላት እናት ጭንቅ ውስጥ ገባች። ልጇ ‘764’ የተባለ ቀኝ ዘመም ሰይጣን አምላኪ ቡድንን ነበር የተቀላቀለችው። ቡድኑ ታዳጊ ሴቶችን መጉዳት የሚፈልጉ ወጣት እና አዋቂ ወንዶችን በዋናነት ይዟል።

የአንገታችን መጠን ስለ ጤናችን ምን ይነግረናል?

የአንገታችን መጠን ስለ ጤናችን ምን ይነግረናል?

ሰኞ 27 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 8:33:05

ፍቅር እና እገታ: ከታሊባን እስር ቤት የወጣው ምሥጢራዊ የስልክ ጥሪ

ፍቅር እና እገታ: ከታሊባን እስር ቤት የወጣው ምሥጢራዊ የስልክ ጥሪ

እሑድ 26 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 5:04:23

የእስልምና እምነታቸው ላይ አጥባቂ የሆኑት የሳፊ ቤተሰቦች የሚጠብቁት ራሳቸው መርጠው ከሚያመጡለት የአፍጋን ሴት ትዳር እንደሚመሠርት ነበር። ሳሚ ደግሞ አይሁዳዊ ነች። አጥባቂ ለሆነው የአፍጋን ሙስሊም ቤተሰብ፤ ልጃቸው የደበቃት አይሁዳዊ ፍቅረኛ እንዳለችው ማወቅ አስደንጋጭ ነበር። የነበረው ሁኔታ ግን እውነታውን እንዲቀበሉ ያስገደደ ነበር።

እየተስፋፋ የመጣውን የካንሰር በሽታን በአመጋገብ መከላከል እና መፈወስ ይቻላል?

እየተስፋፋ የመጣውን የካንሰር በሽታን በአመጋገብ መከላከል እና መፈወስ ይቻላል?

ሰኞ 20 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 4:03:57

የአመጋገብ ለውጥ በማድረግ እና ከመደበኛው ሕክምና ውጪ ያሉ አማራጭ ሕክምናዎችን በመጠቀም ከካንሰር ማገገማቸውን የሚናገሩ አሉ። ለዚህም የተለያዩ ዓይነት ምግቦች፣ ቅመማ ቅመሞች እና እንቅስቃሴዎች በዓለም ዙሪያ ካንሰርን ይከላከላኑ እንዲሁም ይፈውሳሉ በሚል ጥቅም ላይ በስፋት እየዋሉ ነው። በማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይም እየተጋሩ መነጋገሪያ ከሆኑ ሰንበትበር ብለዋል። ባለሙያዎች ምን ይላሉ? እውን ለሕመሙ መፍትሄ ይሰጣሉ?

ከ109 ዓመታት በፊት በጠርሙስ የተላኩ ደብዳቤዎች ተገኙ

ከ109 ዓመታት በፊት በጠርሙስ የተላኩ ደብዳቤዎች ተገኙ

ሐሙስ 30 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 6:02:59

ሁለት አውስትራሊያውያን ወታደሮች የጻፏቸው ደብዳቤዎች ከ109 ዓመታት በኋላ ተገኙ። ጠርሙስ ውስጥ የተገኙት ደብዳቤዎች የተጻፉት በመጀመሪያው የዓለም ጦርነት ወቅት ነበር። ደብዳቤዎቹ የተገኙት በአውስትራሊያ ደቡብ ምዕራብ ባሕር ዳርቻ ነው። ሁለቱ ወታደሮች ጦርነቱን ከመቀላቀላቸው ከቀናት በፊት ደብዳቤ ጽፈው ጠርሙስ ውስጥ አኑረዋል።

“ምርጫ በመጣ ቁጥር እፈራለሁ”

"ምርጫ በመጣ ቁጥር እፈራለሁ"

ቅዳሜ 25 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 7:50:17

በሰውነት ቆዳ፣ በፀጉር እና በዐይን ሜላኒን ሳይኖር ሲቀር የሚከሰተው አልባይኒዝም (albinism) ያለባቸው ታንዛኒያውያን አገር አቀፍ ምርጫን የሚፈሩት ያለ ምክንያት አይደለም። “በተለይ በምርጫ ወቅት አልባይኖዎች ጥቃት ይደርስብናል። ከአልባይኒዝም ጋር በተያያዘ ብዙ የጥንቆላ ዕሳቤዎች አሉ። በጣም ስለምፈራ በምርጫ ቅስቀሳ አልሳተፍም” ትላለች ሜሪያም።

ዓይነ ስውራን ማንበብ እንዲችሉ የሚያደርገው ፈር ቀዳጅ ግኝት

ዓይነ ስውራን ማንበብ እንዲችሉ የሚያደርገው ፈር ቀዳጅ ግኝት

ማክሰኞ 21 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 4:18:14

በተወሰኑ ዓይነ ስውራን ላይ ከዓይን ብሌናቸው ጀርባ በተገጠመላቸው መሳሪያ አማካኝነት ለማንበብ በመቻላቸው በሕወታቸው ላይ ጉልህ ለውጥ ተመዝግቧል። ለንደን በሚገኘው የሙርፊልድስ ዓይን ሆስፒታል ውስጥ በአምስት ታማሚዎች ላይ ይህን ማይክሮ ቺፕን የገጠሙት የቀዶ ሕክምና ሐኪም የዓለም አቀፉ ሙከራው ውጤት “አስደናቂ” መሆኑን ተናግረዋል።

በማጭበርበር የተገኘ 14 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጣ ቢትኮይን ተያዘ

በማጭበርበር የተገኘ 14 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጣ ቢትኮይን ተያዘ

ረቡዕ 15 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 6:07:29

በበይነ መረብ በተፈጸመ ማጭበርበር የተገኘ ነው የተባለ ከ14 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚያወጣ ቢትኮይን መያዙን የአሜሪካ መንግሥት አስታወቀ። ‘ፕሪንስ ግሩፕ’ የተባለ የካምቦዲያ የንግድ ተቋም መስራች የሆነው ቼን ዢ በማጭበርበር ወንጀሉ ተከሷል። የንግድ ሥራው በአሜሪካ እና ዩኬ ዕገዳ ተጥሎበታል። በለንደን ያሉ 19 ቅንጡ መኖሪያዎችም ታግደዋል። ከመኖሪያዎቹ አንደኛው 133 ሚሊዮን ዶላር ያወጣል።

በመካከለኛው ምሥራቅ ኃያል የሆነችው የአይሁዶች አገር እስራኤል እንዴት ተመሠረተች?

በመካከለኛው ምሥራቅ ኃያል የሆነችው የአይሁዶች አገር እስራኤል እንዴት ተመሠረተች?

ማክሰኞ 14 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 3:57:07

በመካከለኛው ምሥራቅ ኃያል እና ብቸኛዋ የአይሁዶች አገር የሆነችው እስራኤል በዙሪያዋ ካሉ አገራት ሁሉ በዕድሜ ትንሿ ናት። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ማብቃት በኋላ በአውሮፓውያኑ 1948 የእስራኤል እንደ አገር መመሥረት በአካባቢው አሁን ድረስ እየተካሄደ ያለ ለውጥን አስከትሏል። ለመሆኑ በየዕለቱ የዓለም መገናኛ ብዙኃን ስሟን ሳያነሱ የማያልፏት ይህች አገር እንዴት ተመሠረተች?

እስራኤል 15 የጦር አውሮፕላኖችን አሰማርታ ኳታር ውስጥ የፈጸመችው ጥቃት

እስራኤል 15 የጦር አውሮፕላኖችን አሰማርታ ኳታር ውስጥ የፈጸመችው ጥቃት

ቅዳሜ 13 ሴፕቴምበር 2025 ጥዋት 4:56:17

በኳታር ዋና ከተማ ዶሃ ውስጥ እስራኤል ጥቃት የፈጸመችው በርካታ የሐማስ ፖለቲካ ቢሮ ባለሥልጣናት በሚኖሩበት የመኖሪያ አካባቢ ላይ ነው። በዚህ ጥቃት አስከ ስምንት የሚደርሱ ፍንዳታዎችን እና ከፍተኛ ጭስ በዶሃ ሰሜናዊ ክፍል ላይ ማየታቸውን ዓይን እማኞች ተናግረዋል። ከጥቃቱ ደቂቃዎች በኋላ ደግሞ እስራኤል ለተፈጸመው ጥቃት በይፋ ኃላፊነቱን ወስዳለች።

የእስራኤል ፕሬዝዳንት እንዲሆን ተጠይቆ የነበረው ታዋቂው የፊዚክስ ሊቅ አልበርት አንስታይን

የእስራኤል ፕሬዝዳንት እንዲሆን ተጠይቆ የነበረው ታዋቂው የፊዚክስ ሊቅ አልበርት አንስታይን

ረቡዕ 20 ኦገስት 2025 ጥዋት 3:56:27

የጠቅላይ ሚኒስትር ዴቪድ ቤን ጉርዮን መንግሥት በዓለም ታዋቂ የሆነው ሳይንቲስት አልበርት አንስታይን ለእስራኤል ፕሬዝዳንትነት እንዲሆን ካጩት በኋላ በዩናይትድ ስቴትስ የእስራኤል አምባሳደር አባ ኢባን አንስታይንን እንዲያነጋግሩ ተደረገ።

ሐማስ በጋዛ ከሚደረገው ጦርነት ተርፎ ኅልውናው ሊቀጥል ይችላል?

ሐማስ በጋዛ ከሚደረገው ጦርነት ተርፎ ኅልውናው ሊቀጥል ይችላል?

ሰኞ 11 ኦገስት 2025 ጥዋት 4:01:11

ሁለት ዓመት ሊሞላው በተቃረበው ጦርነት በጋዛ ሰርጥ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ሲገደሉ የግዛቲቱ አብዛኛው ክፍል ፈራርሷል። እስራኤል ዘመቻዋን ስትጀምር ያስቀመጠቻቸው ታጋቾችን የማስለቀቅ እና ሐማስን የመደምሰስ ዕቅዷ ከግቡ አልደረሰም። ከወዳጆቿ ሳይቀር ተቃውሞ ቢገጥማትም አሁን ደግሞ ጋዛን ሙሉ ለሙሉ የመቆጣጠር ዕቅድ እንዳላት ይፋ አድርጋለች። በርካታ መሪዎቹ የተገደሉበት ሐማስ ከዚህ ጦርነት በኋላ ዕጣ ፈንታው ምን ሊሆን ይችላል?

በእስራኤል ጥቃት እየተፈተኑ በሥልጣን ላይ አንድ ዓመት የሆናቸው የኢራኑ ፕሬዝዳንት

በእስራኤል ጥቃት እየተፈተኑ በሥልጣን ላይ አንድ ዓመት የሆናቸው የኢራኑ ፕሬዝዳንት

ሰኞ 28 ጁላይ 2025 ጥዋት 7:47:12

ማሱድ ፔዜሽኪያን ሐምሌ 2024 የኢራን ፕሬዝዳንት ሆነው ከተሾሙ ከአንድ ቀን በኋላ በቀጥታ ወደ ፖለቲካ እሳት ውስጥ ገብተዋል። ይህም አለመረጋጋት በሌለው በኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ መሪዎች ታሪክ ውስጥ ከታዩት ጅማሪዎች መካከል እጅግ አስደንጋጩ እና በቀውስ የታጀበ ነበር።

በአሜሪካ ድጋፍ የተጀመረው የኢራን የኒውክሌር ፕሮግራም ታሪክ

በአሜሪካ ድጋፍ የተጀመረው የኢራን የኒውክሌር ፕሮግራም ታሪክ

ማክሰኞ 1 ጁላይ 2025 ጥዋት 3:57:49

በአውሮፓውያኑ መጋቢት 5/1957 ዩናይትድ ስቴትስ በወቅቱ በመሐመድ ሬዛ ፓህላቪ ከምትመራው ኢራን ጋር ለሲቪል የአውቶሚክ ኢነርጂ አጠቃቀም የትብብር ስምምነት ተፈራረመች። በ’አተምስ ፎር ፒስ’ መርሃ ግብር ጥላ ስር የነበረው ይህ ስምምነት የኢራንን የኒውክሌር መርሃ ግብር ለመጀመር መሠረት ጣለ። ለዋሽንግተን፣ በዚያ የቀዝቃዛ ጦርነት ወቅት ኢራን ተጨማሪ መስህብ ነበራት።

ከኢትዮጵያ እስከ ኢራን - የእስራኤሉ የስለላ መሥሪያ ቤት ሞሳድ ‘ኦፕሬሽኖች’

ከኢትዮጵያ እስከ ኢራን - የእስራኤሉ የስለላ መሥሪያ ቤት ሞሳድ ‘ኦፕሬሽኖች’

ሐሙስ 19 ጁን 2025 ጥዋት 3:52:56

እስራኤል ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ለአርብ አጥቢያ በፈጸመችው ጥቃት ቁልፍ የሚባሉ የኢራን የጦር አዛዦች እንዲሁም የኒውክሌር ሳይንቲስቶች መገደላቸው ያሉበትን ትክክለኛ ቦታ በተመለከተ መረጃ እንዳላት የሚያሳይ ነው። ከዚህ መረጃ እና ተልዕኮ ጀርባ ደግሞ የአገሪቱ የሥለላ ተቋም ሞሳድ እንዳለ ይታመናል። ሞሳድ ባለፉት ሰባት አስርት ዓመታት ውስጥ ከኢትዮጵያ እስከ ኢራን የፈጸማቸው ዋናዎቹ ተልዕኮዎች የትኞቹ ናቸው?

ከእስራኤል ጥቃት ቀደም ብለው ወደ ኢራን ሰርገው የገቡት የሞሳድ ሰላዮች ምን አደረጉ?

ከእስራኤል ጥቃት ቀደም ብለው ወደ ኢራን ሰርገው የገቡት የሞሳድ ሰላዮች ምን አደረጉ?

ሰኞ 23 ጁን 2025 ጥዋት 3:54:51

…የኢራን ከፍተኛ ጄነራሎች እሰራኤል ጥቃት ልትሰነዝር ትችላለች የሚለው ነገር አሳስቧቸው ስብሰባ ጠሩ። ሁልጊዜም እንደሚያደርጉት ‘የእስራኤል ነገር አይታወቅም’ ብለው ከመሬት ሥር በተዘጋጀ የምድር ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ ገቡ። ሞሳድ ግን ይህን ያውቅ ነበር። ቁልፍ ስብሰባዎች እዚህ ምድር ቤት እንደሚደረጉ መረጃ ነበረው።. . .

እስራኤል እና ኢራን በወታደራዊ አቅም ምን ያህል ተመጣጣኝ ናቸው?

እስራኤል እና ኢራን በወታደራዊ አቅም ምን ያህል ተመጣጣኝ ናቸው?

ዓርብ 13 ጁን 2025 ጥዋት 3:51:33

ኢራን እና እስራኤል ለረጅም ጊዜ በእጅ አዙር እንጂ በቀጥታ ግጭት ውስጥ ገብተው አየውቁም። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን አንደኛው በሌላኛው ላይ የቀጥታ ጥቃት እየፈጸሙ ከጦርነት አፋፍ ላይ መድረሳቸው አሳሳቢ ሆኗል። ለመሆኑ እስራኤል እና ኢራን ጦርነት ውስጥ ቢገቡ ምን ሊከሰት ይችላል? ሁለቱ አገራትስ በወታደራዊ አቅም ምን ያህል ይመጣጠናሉ?

ኢራን እና እስራኤል ለምን ደመኛ ጠላቶች ሆኑ?

ኢራን እና እስራኤል ለምን ደመኛ ጠላቶች ሆኑ?

እሑድ 15 ጁን 2025 ጥዋት 4:51:06

ኢራን ከግብፅ ቀጥላ ለእስራኤል እውቅና በመስጠት ሁለተኛዋ እስላማዊ አገር ነበረች። ነገር ግን ከኢራን እስላማዊ አብዮት በኋላ ይህ ግንኙነት ተበላሽቶ ከአራት አስርታት በላይ በጠላትነት እየተያዩ ቆይተዋል። ለመሆኑ የሁለቱ አገራት ግንኙነት ወደ ደመኛ ጠላትነት ለምን ተሸጋገረ?

አዛዦቹ በእስራኤል ጥቃት የተገደሉበት የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ማን ነው? ምንስ አቅም አለው?

አዛዦቹ በእስራኤል ጥቃት የተገደሉበት የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ማን ነው? ምንስ አቅም አለው?

ቅዳሜ 14 ጁን 2025 ጥዋት 4:31:37

እስራኤል በፈጸመችው ጥቃት በርካታ የአገሪቱ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዦች እና የኒውክሌር ሳይንቲስቶች መገደላቸውን ኢራን አረጋግጣለች። በጥቃቱ የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ የአየር ኃይል አዛዥን ጨምሮ ቢያንስ 20 የኢራን ወታደራዊ ኃይል ከፍተኛ አዛዦች ተገድለዋል። ይህ ኢራን የምትመካበት ወታደራዊ ኃይል ማን ነው? ምንስ አቅም አለው?

በደቡብ ኢትዮጵያ ለሰዎች ሞት ምክንያት የሆነው ማርበርግ ቫይረስ መሆኑ ታወቀ፤ ክትባት ወይም መድኃኒት አለው?

በደቡብ ኢትዮጵያ ለሰዎች ሞት ምክንያት የሆነው ማርበርግ ቫይረስ መሆኑ ታወቀ፤ ክትባት ወይም መድኃኒት አለው?

ዓርብ 14 ኖቬምበር 2025 ከሰዓት 3:38:17

በደቡብ ኢትዮጵያ በጂንካ ከተማ ተከስቶ ለስድስት ሰዎች ሞት ምክንያት የሆነው በሽታ ማርበርግ ቫይረስ መሆኑን የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር አስታወቀ። ከኢትዮጵያ በስተደቡብ በሚገኙ አገራት ውስጥ ተከስቶ የነበረው ይህ በሽታ ከሳምንት በፊት ነው በደቡብ ኢትዮጵያ አካባቢዎች ተከስቶ ሁለት የጤና ባለሙያዎችን ጨምሮ ስድስት ሰዎችን የገደለው።

ፎጣዎቻችን ለተለያዩ በሽታዎች ሊያጋልጡን እንደሚችሉ ያውቃሉ? እንዴት ንጽህናቸውን እንጠብቅ?

ፎጣዎቻችን ለተለያዩ በሽታዎች ሊያጋልጡን እንደሚችሉ ያውቃሉ? እንዴት ንጽህናቸውን እንጠብቅ?

ሐሙስ 13 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 4:03:08

ሰውነታችንን አሊያም እጃችንን የምንደርቅባቸው ፎጣዎች ብዙ ጠቀሜታ ቢሰጡም እግረ መንገዳቸውን ረቂቅ ተህዋስያንን ከሰውነታችን ላይ ያነሳሉ።ፎጣዎቻችን ለምን ዓይነት በሽታዎች ያጋልጡናል? ፎጣዎችን ሳናጥብ ለምን ያህል ጊዜ እንጠቀምባቸዋለን? በምን ያህል ጊዜስ መታጠብ አለባቸወ?

የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት ምንድን ነው?

የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት ምንድን ነው?

እሑድ 9 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 4:58:10

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የእድሳት ሥራው የተጠናቀቀውን የፋሲል ግንብ መርቀዋል። ባለፈው ዓመት የጥገና እድሳት እየተከናወለት በነበረበት ወቅት የግንቡ ታሪካዊ ሽሯሟ ቀለም ነጥቶ መታየቱ በርካታ መላምት እንዲሰጥ አድርጎ ነበር። የታሪካዊው ግንብ ቀለም ለዘመናት ከሚታወቅበት ተለውጦ ለምን ነጣ? የሚል ጥያቄ እንዲነሳም ምክንያት ሆኗል።በጥገና እድሳቱ በአማካሪነት እንዲሁም በጥናት የተሳተፉት አንጋፋው አርክቴክት ፋሲል ጊዮርጊስ በወቅቱ ከቢቢሲ ጋር ቆይታ በማድረግ ለጉዳዩ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

የአንገታችን መጠን ስለ ጤናችን ምን ይነግረናል?

የአንገታችን መጠን ስለ ጤናችን ምን ይነግረናል?

ሰኞ 27 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 8:33:05

እየተስፋፋ የመጣውን የካንሰር በሽታን በአመጋገብ መከላከል እና መፈወስ ይቻላል?

እየተስፋፋ የመጣውን የካንሰር በሽታን በአመጋገብ መከላከል እና መፈወስ ይቻላል?

ሰኞ 20 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 4:03:57

የአመጋገብ ለውጥ በማድረግ እና ከመደበኛው ሕክምና ውጪ ያሉ አማራጭ ሕክምናዎችን በመጠቀም ከካንሰር ማገገማቸውን የሚናገሩ አሉ። ለዚህም የተለያዩ ዓይነት ምግቦች፣ ቅመማ ቅመሞች እና እንቅስቃሴዎች በዓለም ዙሪያ ካንሰርን ይከላከላኑ እንዲሁም ይፈውሳሉ በሚል ጥቅም ላይ በስፋት እየዋሉ ነው። በማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይም እየተጋሩ መነጋገሪያ ከሆኑ ሰንበትበር ብለዋል። ባለሙያዎች ምን ይላሉ? እውን ለሕመሙ መፍትሄ ይሰጣሉ?

ለ20 ደቂቃ በመናፈሻዎች ውስጥ መንሸራሸር ለጤና ያለው ጥቅም

ለ20 ደቂቃ በመናፈሻዎች ውስጥ መንሸራሸር ለጤና ያለው ጥቅም

ዓርብ 10 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 7:10:42

በመናፈሻ ውስጥ ወይም በጫካ ውስጥ ከተንሸራሸሩ በኋላ መረጋጋት ከተሰማዎት፣ ይህ በሃሳብዎ የፈጠሩት አይደለም ፤ ሥነ ሕይወት ነው። ከቤት ውጭ መሆን የጭንቀት ሆርሞኖችን በመቀነስ፣ የደም ግፊትን ከማቃለል አልፎ ተርፎም የሆድ እቃ ጤናን በማሻሻል በሰውነትዎ ውስጥ ሊታይ የሚችል ለውጥ ሊያመጣ ይችላል። እነዚህን ጥቅሞች ለማግኘት ለሰዓታት የእግር ጉዞ ማድረግ አያስፈልግም፤ የቀንዎን 20 ደቂቃ ለዚህ ተግባር ቢያውሉ ለውጡን ያዩታል።

በተፈጥሮ ሒሳብ ሰነፍ የሆኑ ሰዎች አሉ?

በተፈጥሮ ሒሳብ ሰነፍ የሆኑ ሰዎች አሉ?

ዓርብ 10 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 4:00:02

ለአንዳንዶች ሒሳብ በቀላሉ የሚሠራ ሲሆን፣ ሌሎች ግን ቀላል የሚባለው ስሌት ሳይቀር ይፈትናቸዋል። ይህ ከዘረ መል ጋር እንደሚያያዝ ባለሙያዎች ይናገራሉ። ነገሩ የዘረ መል ብቻ ግን አይደለም። ከሥነ ሕይወት፣ ከሥነ ልቦና እና አካባቢ ጋር ይተሳሰራል። ለመሆኑ በተፈጥሮ ሒሳብ ሰነፍ የሆኑ ሰዎች አሉ?

ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት የምትገኘው አሊ ዶሮ እና አካባቢዋ ለምን የእገታ ማዕከል ሆኑ?

ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት የምትገኘው አሊ ዶሮ እና አካባቢዋ ለምን የእገታ ማዕከል ሆኑ?

ረቡዕ 4 ጁን 2025 ጥዋት 4:00:19

ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ውስጥ በሕዝብ እና በጭነት ተሽከርካሪዎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች እና እገታዎች ተበራክተዋል። ይህ ክስተት ደግሞ ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት ላይ በሚገኘው የሰሜን ሸዋ አካባቢ በተደጋጋሚ ሲከሰት ቆይቷል። በተለይ አሊ ዶሮ የሚባለው ቦታ የጥቃት እና የእገታ ማዕከል ሆኗል እየተባለ ነው። ቢቢሲ በተለይ ይህ ቦታ ለምን የመንገደኞች እና የአሽከርካሪዎች ‘የሞት ቀጣና’ ሆነ? በሚል ለወራት የዘለቀ ምርመራ አድርጓል።

”. . . ከምድሩ ይልቅ የሰማዩን መንገድ ለመምረጥ ተገደናል” እገታ ያሰጋቸው መንገደኞች

". . . ከምድሩ ይልቅ የሰማዩን መንገድ ለመምረጥ ተገደናል" እገታ ያሰጋቸው መንገደኞች

ሰኞ 12 ሜይ 2025 ጥዋት 4:02:02

ባለፉት ዓመታት በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች ውስጥ የሚካሄዱ ግጭቶች እና በታጣቂዎች የሚፈጸሙ እገታዎች ዜጎች በፈለጉት ጊዜ እና መንገድ በአገሪቱ ውስጥ እንዳይንቀሳቀሱ ብርቱ ስጋት ፈጥሮባቸዋል። በተለይ ደግሞ የመንገደኞች ማጓጓዣ ተሽከርካሪዎችን በማድረግ የሚፈጸሙት ያላባሩ እገታዎች በዋነኞቹ የአገሪቱ ክልሎች ውስጥ እንቅስቃሴን አዳጋች አድርገውታል። በዚህም ሳቢያ አቅሙ ያላቸው እና የግድ የሆነባቸው ሰዎች ፊታዎችን ወደ አየር ትራንስፖርት አዙረዋል።

የአእምሮ ዕድገት መዛባት (ኦቲዝም) ያለባቸው መኪና እንዲያሽከረክሩ የሚረዳ ጥናት ለኳታር ያቀረቡት ኢትዮጵያዊ ተመራማሪ

የአእምሮ ዕድገት መዛባት (ኦቲዝም) ያለባቸው መኪና እንዲያሽከረክሩ የሚረዳ ጥናት ለኳታር ያቀረቡት ኢትዮጵያዊ ተመራማሪ

ረቡዕ 2 ኤፕሪል 2025 ጥዋት 4:04:10

ዛሬ፣መጋቢት 24 የኦቲዝም ግንዛቤ ማስጨበጫ ቀን ነው። ይህ ዕለት በዓለም ደረጃ ታስቦ እንዲውል ለተባበሩት መንግሥታት ሐሳብ ያቀረበችው ኳታር ናት። ወደዚያው ብናቀና ዶክተር ወንድወሰን ግርማን እናገኛለን። ኦቲስቶች መኪና እንዲያሽከረክሩ የሚያስችል ከፍተኛ ምርምር ያደረጉ ኢትዮጵያዊ ናቸው።

‘ዝምተኛው ገዳይ’ በኢትዮጵያ

'ዝምተኛው ገዳይ' በኢትዮጵያ

ዓርብ 28 ማርች 2025 ጥዋት 4:04:02

የዓለም ጤና ድርጅት የኢትዮጵያ የአየር ብክለት ልኬት ከፍተኛ መሆኑን ያሳያል። ድርጅቱ እንደሚለው 99 በመቶው የዓለም ሕዝብ የሚተነፍሰው አየር ተበክሏል። ተላላፊ ላልሆኑ በሽታዎች የሚዳርገው የአየር ብክለት በኢትዮጵያ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ቢቢሲ ያነጋገራቸው ባለሙያ ይናገራሉ። ለመሆኑ በኢትዮጵያ ዋነኛ አየር በካዮች የትኞቹ ናቸው? መፍትሔውስ ምንድን ነው?

"’ቁርጭምጭሚት’ የሚለው ቃል ያስቀኛል’’ ለ23 ዓመታት ለፈረንጆች አማርኛን ያስተማረችው ፖላንዳዊት፣ ዶ/ር ኤቫ ቮልክ-ሶሬ

"'ቁርጭምጭሚት' የሚለው ቃል ያስቀኛል'' ለ23 ዓመታት ለፈረንጆች አማርኛን ያስተማረችው ፖላንዳዊት፣ ዶ/ር ኤቫ ቮልክ-ሶሬ

ዓርብ 7 ማርች 2025 ጥዋት 3:50:04

ፓላንዳዊቷ ዶ/ር ኤቫን የአማርኛ ቋንቋን ከ40 ዓመት በፊት ተምራ በዲግሪ ከተመረቀች በኋላ ከሃያ ዓመታት በላይ በማስተማር በርካቶችን በአማርኛ ቋንቋ ዲግሪ አስይዛለች። የምታስተምርበት ዩኒቨርስቲ ወደ 80 ዓመታት ለሚጠጋ ጊዜ አማርኛን እያስተማረ ነው። አማርኛ ቋንቋን “ፏፏቴ ነው” የምትለው ዶ/ር ኤቫን በአገሯ በአማርኛ አስተርጓሚነት ትሠራለች። ለመሆኑ እንዴት ከአማርኛ ጋር ተዋወቀች?

“ብልጽግናዎች ይዘውን እንዲጠፉ አንፈቅድም፤ አገራችን ሕዝባችን ነው፤ ዝም አንላቸውም” - ጃዋር መሐመድ

"ብልጽግናዎች ይዘውን እንዲጠፉ አንፈቅድም፤ አገራችን ሕዝባችን ነው፤ ዝም አንላቸውም" - ጃዋር መሐመድ

ሐሙስ 19 ዲሴምበር 2024 ጥዋት 4:54:19

በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ጉልህ ስፍራ ካላቸው ፖለቲከኞች መካከል ጃዋር መሃመድ አንዱ ነው። ለዓመታት ያህል በኦሮሚያ የነበሩ ትግሎችን እንዲሁም ተቃውሞዎችን ከጀርባም ሆነ ከፊት ሆኖ በማስተባበር እና በመምራት ግንባር ቀደም ነው።የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ፓርቲ አመራሩ ጃዋር ከትውልድ አንስቶ በፖለቲካ ህይወቱ የተጓዘበትን ህይወቱ ላይ የሚያጠነጥን ‘አልጸጸትም’ የተሰኘውን መጽሐፍ ታህሳስ 10/ 2017 ዓ.ም በኬንያዋ መዲና ናይሮቢ ያስመርቃል። ጃዋር መሃመድ በአገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ፣ በቀጣይ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ስለሚኖረው ሚና፣ አገሪቱ ስላለችበት ሁኔታ ከቢቢሲ አማርኛ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ሙዝ በዳቦ እየበሉ ‘ፒኤችዲ’ የሚማሩ የዩኒቨርስቲ መምህራን ሰቆቃ

ሙዝ በዳቦ እየበሉ 'ፒኤችዲ' የሚማሩ የዩኒቨርስቲ መምህራን ሰቆቃ

ሰኞ 30 ሴፕቴምበር 2024 ጥዋት 4:13:42

ይህ ጥናታዊ ዘገባ የዩኒቨርስቲ መምህራን ላይ ያጠነጥናል፤ ከእነርሱም ውስጥ ፒኤችዲ (ዶክትሬት) የሚማሩት ላይ ያተኩራል። መምህራኑ የበለጠ በተማሩ ቁጥር የበለጠ እየተራቡ እንደሆነ ያወሳሉ። ቢቢሲ በርከት ያሉ የፒኤችዲ ተማሪዎችን ለወራት ቃለ መጠይቅ ሲያደርግ ቆይቷል። ከጉዳዩ ስፋት የተነሳ የብዙዎቹ አስቸጋሪ የኑሮ ሁኔታ እና ታሪክን በሚወክሉ በአምስት መምህራን ተወክሎ ቀርቧል።

“ሰው መሃል ሆኜ ሁሉም ጨካኝ ሆኖብኝ ነበር” - የፀጋ በላቸው ዘጠኝ የጠለፋ ቀናት

“ሰው መሃል ሆኜ ሁሉም ጨካኝ ሆኖብኝ ነበር” - የፀጋ በላቸው ዘጠኝ የጠለፋ ቀናት

ሰኞ 18 ኖቬምበር 2024 ጥዋት 3:53:07

ግንቦት 2015 ዓ.ም. የተፈጸመው የፀጋ በላቸው ጠለፋ ብዙዎችን ያስቆጣ፣ መነጋገሪያም የሆነ የወንጀል ድርጊት ነበር። ፀጋ፤ ከአንድ ዓመት ከመንፈቅ በፊት ተጠልፋ ያሳለፈቻቸውን ቀናት በተመለከተ ለመጀመሪያ ጊዜ ለቢቢሲ በዝርዝር ተናግራለች። ከቢቢሲ ጋር በነበራት ዘለግ ያለ ቆይታ፤ ስለተጠለፈችበት መንገድ እና ስላሳለፈቻቸው ዘጠኝ ቀናት በዝርዝር ተርካለች። ከጠለፋው ነጻ የወጣችበት መንገድም አስቀድሞ በክልሉ መንግሥት ከተገለጸው የተለየ እንደሆነ ለመጀመሪያ ጊዜ ተናግራለች። ለምን ከኢትዮጵያ እንደተሰደደች እና ስለ ቀጣይ ዕቅዶቿም እንዲሁ አጋርታለች።

በአንድ ወቅት ኢትዮጵያ ክፉኛ አቁስላ፣ ማርካ ያከመችው የጁባላንዱ ፕሬዚዳንት ማዶቤ

በአንድ ወቅት ኢትዮጵያ ክፉኛ አቁስላ፣ ማርካ ያከመችው የጁባላንዱ ፕሬዚዳንት ማዶቤ

ሰኞ 17 ማርች 2025 ጥዋት 3:41:37

“የብዙ ኢትዮጵያዊ ደም ነው የወሰደው። የኢትዮጵያ ደም ነው ያለህ እንለዋለን” ይህ በሶማሊያ የኢትዮጵያ የቀድሞ አምባሳደር ወንድሙ አሳምነው ለአሁኑ የጁባላንድ ግዛት ፕሬዚዳንት ማዶቤ በቀልድ መልኩ ጣል ያደርጉላቸው ነገር ነው። ይህ በቀልድ የተለወሰ መሪር እውነታ ነው። እውነታው የሶማሊያዋን ራስ ገዝ ጁባላንድን ላለፉት 12 ዓመታት ያስተዳደረው ማዶቤ በአንድ ወቅት በኢትዮጵያ ጦር ክፉኛ ቆስሎ በአዲስ አበባ ህክምና አድርጓል።

ዕድገት በኅብረት ዘመቻ፡ የሦስቱ ጓደኛሞች የ50 ዓመታት ትዝታ

ዕድገት በኅብረት ዘመቻ፡ የሦስቱ ጓደኛሞች የ50 ዓመታት ትዝታ

ቅዳሜ 19 ኤፕሪል 2025 ጥዋት 4:57:24

ወታደራዊው አስተዳደር ደርግ የአገሪቱን የመሪነት መንበር ከያዘ በኋላ የዛሬ 50 ዓመት የዕድገት በኅብረት ዘመቻን አወጀ። በዚህም ከ10ኛ ክፍል እስከ ዩኒቨርስቲ ያሉ ተማሪዎች እና መምህራን በገጠሪቱ ኢትዮጵያ ተሰማርተው በማስተማር እና በልማት ሥራዎች ላይ እንዲሳተፉ አድርጎ ነበር። በዚህ ዘመቻ የተሳተፉ የዚያ ዘመን አፍላ ወጣቶች ከአምስት አሥርታት በኋላ በጋራ ተሰባስበው ያሳለፉትን ጊዜ አስታውሰዋል። ትዝታቸውንም ለቢቢሲ አጋርተዋል. . .

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ከበሮ እና ጽናጽልን ሌሎች ቤተ እምነቶች እንዳይጠቀሙ መከልከል ትችላለች?

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ከበሮ እና ጽናጽልን ሌሎች ቤተ እምነቶች እንዳይጠቀሙ መከልከል ትችላለች?

ቅዳሜ 3 ሜይ 2025 ጥዋት 4:55:41

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የከበሮ፣ ጽናጽል እና መቋሚያ ንድፎችን በአዕምሯዊ ንብረትነት ማስመዝገቧን ተከትሎ ጉዳዩ ሲያከራክር ሰንብቷል። ምዝገባው ሌሎች ቤተ እምነቶች እነዚህን መገልገያዎች “እንዳይጠቀሙ የመከልከል መብት ይሰጣል ወይስ አይሰጥም?” የሚለው የክርክሩ ማጠንጠኛ ሆኗል። በዚህ ጉዳይ ላይ የቤተ ክርስቲያኗ ኃላፊዎች ያላቸው አረዳድ እና የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን አቋም የተለያየ ነው።

በአርሰናል ‘ፍቅር የወደቁት’ የ65 ዓመቷ እናት፡ ወይዘሮ እቴቱ ማሞ

በአርሰናል ‘ፍቅር የወደቁት’ የ65 ዓመቷ እናት፡ ወይዘሮ እቴቱ ማሞ

ዓርብ 24 ሜይ 2024 ጥዋት 4:16:17

ከእንግሊዝ ታላላቅ ቡድኖች መካከል አንዱ የሆነው የአርሰናል የልብ ደጋፊ የሆኑት ወ/ሮ እቴቱ ማሞ የ65 ዓመት እናት ናቸው። ላለፉት 20 ዓመታት አርሰናልን ያለማቋረጥ ደግፈዋል። እንደብዙዎቹ የቡድኑ ደጋፊዎች ዘንድሮ አርሰናል ዋንጫ ባለማንሳቱ ቢከፉም ድጋፋቸው ግን እንደሚቀጥል ይናገራሉ። ከሁሉም ተጫዋቾች ይልቅ እሳቸው ገብረኢየሱ ለሚሉት ለጋብሬል ጀሱስ እና ለቡካዮ ሳካ የተለየ ፍቅር አላቸው።