
__
የአውሮፓ አገራት አሜሪካ በኢራን ላይ ለምታካሂደው ወታደራዊ ጥቃት የጦር አውሮፕላኖቿ የአየር ክልላቸውን እንዳይጠቀሙ እየከለከሉ ነው። እንዲህ ያለው ውሳኔ በስፔን የተጀመረ ሲሆን፣ አሁን ደግሞ ፈረንሳይ እና ጣልያን ተመሳሳይ አቋም መያዛቸው እየተዘገበ ነው።

ሰኞ 30 ማርች 2026 ጥዋት 9:48:57
በኢትዮጵያ የተፈጠረውን የነዳጅ እጥረት ተከትሎ የአንዳንድ መንግሥት መሥሪያ ቤት ሠራተኞች የዓመት እረፍት እንዲወጡ እየተደረገ መሆኑን ቢቢሲ ያነጋገራቸው ሠራተኞች ተናገሩ።

ሰኞ 30 ማርች 2026 ጥዋት 8:02:30
በቢቢሲ የተረጋገጡ ፎቶዎች እንደሚያሳዩት የአሜሪካ ወታደራዊ የዕዝ እና የቁጥጥር አውሮፕላን በሳዑዲ አረቢያ በሚገኝ የአየር ኃይል ሰፈር ውስጥ በኢራን በተፈጸመበት ጥቃት ተመትቶ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበታል። በጦርነቶች ውስጥ አውሮፕላኑ ሚና ምን ያህል ወሳኝ ነው?

ሰኞ 30 ማርች 2026 ጥዋት 3:50:14
ኢራን አሜሪካ እና እስራኤል ጥቃት ከከፈቱባት ቀን አንስቶ ከፍተኛውን ጥቃት ከእስራኤል ይልቅ በዙሪያዋ ባሉ አረብ አገራት ላይ ነው የፈፀመቸው። ከእነዚህም መካከል የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ዋነኛዋ የኢራን ጥቃት ዒላማ ሆና ዋጋ እየከፈለች ነው።

ዓርብ 27 ማርች 2026 ጥዋት 3:59:27
የዓለም ጤና ድርጅት በአውሮፓውያኑ በ2021 ባወጣው አሃዝ መሠረት በመላው ዓለም ከ127 ሰዎች መካከል አንዳቸው ኦቲዝም እንዳለበት/እንዳለባት ያሳያል። አነስተኛ እና መካከለኛ ገቢ ባላቸው አገራት በቂ መረጃ ባይገኝም፤ ለአእምሮ ዕድገት መዛባት ያለው ተጋላጭነት በየአገሩ የተለያየ መሆኑ ተስተውሏል።

ረቡዕ 25 ማርች 2026 ጥዋት 3:53:27
የመካከለኛው ምሥራቅ ጦርነት ከነዳጅ ሃብት ጋር ሊያያዝ እንደሚችል የሚገመት ጉዳይ ነው። አሜሪካ እና እስራኤል ከኢራን ጋር የሚያደርጉት ጦርነት እየተስፋፋ መሄዱን ተከትሎ ውሃም ሌላኛው የግጭቱ ማዕከል ሊሆን እንደሚችል እየተነገረ ነው። እንዴት?

ዓርብ 27 ማርች 2026 ጥዋት 3:57:49
ገዢው ብልጽግና ፓርቲ ዕጩ ባላቀረበባቸው ከ80 በላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫዎች ውስጥ የተቃዋሚዎቹ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) እና የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) አመራሮች የሚወዳደሩባቸው የምርጫ ክልሎች እንደሚገኙ ቢቢሲ ተገንዝቧል።

ረቡዕ 25 ማርች 2026 ጥዋት 11:33:30
በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች አዲስ የመለያ ሠሌዳ ቁጥር ለመስጠት የተዘጋጀው የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የተለዩ የሠሌዳ ቁጥሮችን በጨረታ ሊሰጥ ነው። ሚኒስቴሩ በመላው አገሪቱ የተሽከርካሪዎች የሠሌዳ ቁጥርን ለውጥ ለማድረግ የሚያስፈልገውን ዝግጅት ማጠናቀቁን እና በቅርቡም አዲሱን የሠሌዳ መለያ ቁጥር (ታርጋ) መስጠት እንደሚጀምር እስታውቋል።

ዓርብ 27 ማርች 2026 ጥዋት 11:29:08
ብልጽግና ፓርቲ፤ ምርጫ የመካሄዱ ነገር አጠራጣሪ በሆነበት ትግራይ ክልል ለሚገኙ የፓርላማ እና የክልል ምክር ቤት መቀመጫዎች አንድም ዕጩ አለማቅረቡን ቢቢቢ የተመለከተው የዕጩዎች ዝርዝር ያሳያል። ስድስት ተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች እና ሁለት ቅንጅቶች በበኩላቸው 101 ዕጩዎችን አስመዝግበዋል።

ረቡዕ 25 ማርች 2026 ከሰዓት 12:34:07
ብልጽግና ፓርቲ ግንቦት ላይ ይካሄዳል ተብሎ በሚጠበቀው ሰባተኛው አጠቃላይ ምርጫ ለአዲስ አበባ ከተማ ካቀረባቸው 154 ዕጩዎች ውስጥ 96 ያህሉ በባለፈው ምርጫ በመዲናዋ ያልተወዳደሩ እንደሆኑ ቢቢሲ ያደረገው ዳሰሳ ያሳያል። በመጪው ምርጫ በአዲስ አበባ ዕጩ ሆነው ካልቀረቡት ተመራጮች መካከል ምክትል ከንቲባው ጃንጥራር አባይ ይገኙበታል።

ቅዳሜ 28 ማርች 2026 ከሰዓት 12:20:28
የፊንቴክ ኢንቨስትመንት ድርጅትን “ባልተገባ” እና “በተጋነነ መልኩ” አስተዋውቀዋል እንዲሁም በሕገወጥ መንገድ ከተሰበሰበው ገንዘብ “ተጋሪ” በመሆን ተጠርጥረዋል የተባሉ ታዋቂ ግለሰቦች እና የማስታወቂያ ባለሙያዎች በቁጥጥር ስር አውሎ ፍርድ ቤት ማቅረቡን የፌደራል ፖሊስ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ዛሬ በይፋዊ የፌስቡክ ገጹ ላይ ባወጣው መግለጫ ከ1200 በላይ ዜጎችን አጭበርብረው የ1.7 ቢሊዮን ብር ጉዳት አድርሰዋል ያላቸውን የፊንቴክ ኢንቨስትመንት መስራች እና ባለቤቶች ላይ ምርመራ አጣርቶ አቃቤ ሕግ ክስ መመስረቱን ገልጿል።

ማክሰኞ 17 ማርች 2026 ጥዋት 3:52:07
ከሦስት አስርት ዓመታት በላይ በእርስ በርስ ጦርነት እና ባለመረጋጋት ውስጥ በምትገኘው ሶማሊያ እየተፋለመችው ካለው የአገር ውስጡ አልሻባብ በተጨማሪ ዓለም አቀፍ ታጣቂ ቡድን እግሩን አስገብቷል። በአሁኑ ወቅት እስላማዊ መንግሥት (አይኤስ) ከተባለው የሽብር ቡድን ጋር እየተፋለመች ነው። ይህ ቡድን ኢትዮጵያን ጨምሮ ከተለያዩ አገራት ተዋጊዎችን እየመለመለ ያሰልፋል።

ቅዳሜ 21 ማርች 2026 ጥዋት 11:12:32
የፋኖ ኃይሎች በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ዞን ስር በሚገኙ “የሥራ ኃላፊዎች እና የፀጥታ መዋቅር” ላይ በፈጸሙት ጥቃት ቁጥራቸው ያልተገለጸ ባለሥልጣናት መገደላቸውን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ። ቢቢሲ ያነጋገራቸው አንድ የደቡብ ጎንደር ዞን አስተዳደር ምንጭ፤ የወረዳ ዋና አስተዳዳሪዎችን ጨምሮ ቢያንስ አምስት የአካባቢው ባለሥልጣናት እንደተገደሉ ገልጸዋል።

ቅዳሜ 14 ማርች 2026 ጥዋት 4:30:41
የአፍሪካ ዋንጫ በሚቀጥለው የአውሮፓውያኑ ዓመት በኬንያ፣ በታንዛኒያ እና በኡጋንዳ በጥምረት ይዘጋጃል። የአፍሪካ ዋንጫ በ2028 ድጋሚ ይካሄዳል። ይህ በየሁለቱ ዓመቱ የሚዘጋጀው የአህጉሪቱ የእግር ኳስ ውድድር የመጨረሻው መርሃ ግብር ይሆናል። ካፍ ከ2028 በኋላ ውድድሩን በየአራት ዓመቱ ለማድረግ ወስኗል። ኢትዮጵያ ለብቻዋ ደቡብ አፍሪካ እና ቦትስዋና ደግሞ በጥምር የ2028ቱን የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት ያላቸውን ፍላጎት ይፋ አድርገዋል። ለመሆኑ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ከሁለት ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ የማዘጋጀት አቅም አላት? ካፍ የሚጠይቀው መስፈትስት ምንድነው?

ረቡዕ 11 ማርች 2026 ጥዋት 12:00:00
አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ ጥቃት መክፈታቸውን ተከትሎ በመካከለኛው ምሥራቅ ውስጥ ጦርነት እየተካሄደ ነው። ኢራን እየተፈጸመባት ላለው ጥቃት አጸፋውን በቀጣናው ባሉ የአሜሪካ ወዳጅ አገራት ላይ እየፈጸመች ነው። ለዚህ ደግሞ ኢራን ርካሽ እና ውጤታማ የሆኑትን ሻሂድ-136 የተባሉ አጥፍቶ ጠፊ ድሮኖችን በስፋት እየተጠቀመች ነው። ይህ በምሥል እና በቪዲዮ የተደገፈው ዘገባ ስለድሮኖቹ ምንነት ይተነትናል።

ዓርብ 13 ማርች 2026 ጥዋት 9:54:38
የአሜሪካ ኢሚግሬሽን እና ጉምሩክ ሕግ አስፈጻሚ መሥሪያ ቤት “ራሱን የፋኖ አባል አድርጎ” የገለጸን ሰለሞን ቦጋለ የተባለ ግለሰብ ወደ ኢትዮጵያ ማባረሩን አስታውቋል። የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በስደተኞች እና ጥገኝነት ጠያቂዎች ላይ እየወሰደ ያለውን ጠንካራ እርምጃዎች የሚያስፈጽመው ይህ መሥሪያ ቤት፤ ከትግራይ ጦርነት ጋር በተያያዘ ግለሰቡ ላይ ከባድ ውንጀላዎችን አቅርቧል።

ረቡዕ 11 ማርች 2026 ጥዋት 8:04:25
ላለፉት ሰባት ዓመታት ገደማ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽነር ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩት ጌቱ አርጋው እና ሁለት ምክትል ኮሚሽነሮች ከኃላፊነት ተነሱ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተነሱት አመራሮች ምትክ የቀድሞው የመከላከያ የምድር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናንት ጄነራል አስራት ደኔሮን እና ሁለት ምክትል ኮሚሽነሮችን ሾመዋል።

ዓርብ 13 ማርች 2026 ጥዋት 3:59:24
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት በጄነራል አል ቡርሐን ከሚመራው የሱዳን ጦር ሠራዊት ጋር ግንኙነት ያለውን የሱዳኑን ሙስሊም ብራዘርሁድ ቡድን በተለየ ሁኔታ ዓለም አቀፍ ሽብርተኛ በማለት ከመጋቢት 7/2018 ዓ.ም. ጀምሮ ደግሞ የውጭ የሽብር ቡድን በሚል እንደፈረጀው አስታውቋል። ለመሆኑ ይህ ቡድን ማን ነው? በሱዳን ውስጥስ ያለው ሚና ምን ያህል ነው?

ማክሰኞ 10 ማርች 2026 ጥዋት 3:59:47
በአማራ ክልል፣ ደቡብ ወሎ ዞን፣ በመሐል ሳይንት ወረዳ በሚገኘው ርዕሰ አድባራት ወታዕካ ነገሥት አትሮንሰ ማርያም ገዳም ላይ በተፈጸመ “የከባድ መሣሪያ ጥቃት” ስድስት ሰዎች እንደተገደሉ እና ከ20 በላይ ሰዎች እንደተጎዱ የገዳሙ አስተዳዳሪ እና የዐይን እማኞች ለቢቢሲ ገለጹ።

ሰኞ 9 ማርች 2026 ጥዋት 4:37:59
ቱርክ እና እስራኤል በዓለም አቀፉ የፖለቲካ መድረክ በተቃርኖ የሚንቀሳቀሱ አገራት ናቸው። ኢትዮጵያ ደግሞ ከሁለቱም አገራት ጋር የረዥም ጊዜ ወዳጅነት አላት። ለመሆኑ ኢትዮጵያ ሁለት ተቃራኒ አቋም ያላቸውን አገራት ፍላጎት እንዴት ማጣጣም ትችላለች? ኢትዮጵያ ካሏት ፖለቲካዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ፍላጎቶች አንጻርስ ከየትኛው አገር ጋር ብትወዳጅ የበለጠ ታተርፋለች?

ሐሙስ 26 ማርች 2026 ጥዋት 4:05:53
አንድ ወር ሊሞላው በተቃረበው ጦርነት ከሞላ ጎደል አብዛኞቹ የኢራን ቁልፍ ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ መሪዎች ተገድለዋል። ነገር ግን ኢራን ከአሜሪካ እና ከእስራኤል ጋር የምታደርገውን ፍልሚያ እንዲሁም በመካከለኛው ምሥራቅ አገራት ላይ የምትፈጽመውን ጥቃት ቀጥላለች። ከከባድ ውድመት እና የመሪዎቿ ግድያ በኋላ ኢራን በእነማን እየተመራች ነው?

ረቡዕ 18 ማርች 2026 ጥዋት 3:45:42
አሜሪካ እና እስራኤል ኢራን ላይ ጥቃት ከፍተው ቴህራን ያለአጋር ብቻዋን ሁለቱን ኃያላን እየተጋፈጠች ነው። በዚህ ጊዜ በኢራን የሚደገፈው እና በቀይ ባሕር ላይ ዋነኛ ስጋት የሆነው የየመኑ ታጣቂ ቡድን ሁቲ ባልተለመደ መልኩ እራሱን ያቀበ ይመስላል። እስራኤል በሐማስ ላይ ጥቃት ስትከፍት ፈጥኖ ምላሽ የሰጠው ሁቲ ኢራን ስትጠቃ ለምን ዝምታን መረጠ?

ሰኞ 16 ማርች 2026 ጥዋት 4:02:13
ወታደራዊ ጥቃት የመፈጸም ኃይልን የተመለከቱ ውይይቶች በሚነሱባቸው ወቅቶች አሜሪካ እና እስራኤል እንዴት ኢራንን እያጠቁ እንደሆነ በምሥል ጭምር ከማሳየት ወደ ኋላ አይሉም። በባለሙያ የተዘጋጁ ፎቶዎች እና ቪዲዮዎችን የሚጠቀመው የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ፤ ጥቅም ላይ እየዋሉ ያሉ የመሣሪያ፣ የጄት እና የመርከብ ዓይነቶችን የሚያሳዩ ልጥፎችን በየአጭር ሰዓት ልዩነት ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ይለጥፋል።

ረቡዕ 4 ማርች 2026 ጥዋት 4:35:18
አሜሪካ እና እስራኤል በፈጸሙት ጥቃት የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሜኒ ሲገደሉ፤ ኢራን በመካከለኛው ምሥራቅ አገራት ላይ ጥቃት መፈጸም ቀጥላለች። እየተካሄደ ስላላው ጦርነት፣ ስለ ኢራን እና ባለፉት ቀናት ስለተከሰቱ ዋና ዋና ነገሮች ሊያውቋቸው የሚገቡ እውነታዎች በምሥል እዚህ ይመልከቱ።

ማክሰኞ 3 ማርች 2026 ጥዋት 3:55:19
ሄዝቦላህ መልከ ብዙ ነው። የፖለቲካ ፓርቲ ብቻ አይደለም። ማኅበራዊ አገልግሎት ላይ ይሠራል፣ ፖለቲካ ላይ ይሳተፋል፤ ሚሊሻም ነው። ድንበር ተሻጋሪ ወታደራዊ ክንፍም አለው። ይህ መልከ ብዙነቱ በሊባኖስም ከሊባኖስ ውጪም አቅም ፈጥሮለታል። ለመሆኑ ሄዝቦላህ ማን ነው? እንዴትስ ለእስራኤል ፈተና ሊሆን ቻለ?

እሑድ 15 ማርች 2026 ጥዋት 4:51:50
ዱባይ ከተለያዩ አገራት የመጡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የውጭ ዜጎች መኖሪያ ናት። ከተማዋ ለአስርተ ዓመታት ሰላሙ በሚዋዥቀው ቀጣና ውስጥ የመረጋጋት እና የደኅንነት ተምሳሌት ሆና ታይታለች። በቅርብ ዓመታት ውስጥ ግጭቶች አብዛኛውን የቀጣናውን ክፍል መልክ ቢቀይሩም፤ ዱባይ በአብዛኛው ሳትነካ ቆይታለች። የኢራን ጦርነትን መጀመር ተከትሎ ግን ይህ ገጽታዋ ፈተና ውስጥ ወድቋል።

እሑድ 8 ማርች 2026 ጥዋት 4:54:26
ብርሃኔ የመንግሥታቱ ድርጅት የሕፃናት ስምምነት ላይ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን የሚከለክሉ አንቀፆችን አርቅቀዋል፤ በስምምነቱ እንዲካተቱቱም ውትወታ አድርዋል። የሰብዓዊ መብት አርበኛ የሆኑት ወ/ሮ ብርሃኔ 60 ዓመታት የዘለቀ ስኬታማ ትዳርም አላቸው። ወ/ሮ ብርሃኔ አስፋው ለሴቶች ጤና እና ደኅንነት ላበረከቱት አስተዋፅኦ በሽልማት ተንበሽብሸዋል። ድርጅታቸውን አቋቁመው ከተለያዩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጋር ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ለማስቆም ሲታትሩ ያዩ ደግሞ ለኖቤል አጭተዋቸዋል። ቢቢሲ ወ/ሮ ብርሃኔን ስለ ሥራ እና ሕይወታቸው አነጋግሯቸዋል።

ዓርብ 27 ፌብሩዋሪ 2026 ጥዋት 4:11:37
ለእስልምና እና ለክርስትና እመነት ተከታዮች ዋነኞቹ የፆም ወቅት የሆኑት ረመዳን እና ዓቢይ ፆሞች ተጀምረዋል። የሁለቱም እምነቶነቶች ምዕመናን የፆሙን ጊዜ በየራሳቸው ሥርዓት እና ደንብ መሠረት የሚከውኑት ሲሆን፣ በየዕለቱ ለረጅም ሰዓታት ከምግብ እና ከውሃ ርቀው ይቆያሉ። በዚህ ጊዜ ታዲያ ፆም በሰውነት ላይ ምን ለውጥን ያስከትላል? ምንስ ጥቅም አለው?

ሐሙስ 19 ፌብሩዋሪ 2026 ጥዋት 3:59:37
ግጭቶች በሰው ሕይወት እና አካል እንዲሁም በንብረት እና በመሠረተ ልማቶች ላይ ከሚያደርሱት ጉዳት ባሻገር በሰዎች አካላዊ እና ሥነ ልቦናዊ ጤና እና ደኅንነት ላይ ከባድ ተጽእኖን እንደሚያስከትል ባለሙያዎች ይናገራሉ። እንዲህ ባለው ሁኔታ ውስጥ ስንሆን የሚከሰቱ ሥነ ልቦናዊ ለውጦች ምንድን ናቸው? ለመቋቋምስ ምን ማድረግ እንችላለን?

ዓርብ 20 ማርች 2026 ጥዋት 3:47:34
በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ ቅዱስ የሆነው የረመዳን ወር የጾም ወቅት ተጠናቆ ዛሬ የዒድ አል ፈጥር በዓል ነው። እምነቱ የጨረቃ ዑደት ላይ የተመሠረተ የቀን አቆጣጠር ስለሚጠቀም የረመዳን ወር የሚጀመርበት ጊዜ በየዓመቱ ይቀያየራል። እንዲሁም የጾሙ ወቅት መጠናቀቂያ ዕለትም የሚወሰነው በዚሁ ሂደት ነው። በረመዳን ወር አብዛኞቹ የእምነቱ ተከታዮች በየቀኑ ጀምበር ወጥታ እስከምትጠልቅ ድረስ ከ29 እስከ 30 ለሚሆኑ ቀናት ይጾማሉ።

እሑድ 15 ፌብሩዋሪ 2026 ጥዋት 4:55:55
በመቶዎች ከሚቆጠሩ ዓመታት በኋላ ደጋፊዎቹ ሁለቱንም የዓለም ጦርነቶች፣ የሂሮሺማ እና የናጋሳኪ የኒውክሌር ፍንዳታዎችን፣ የሂትለርን መነሳት እና የኮቪድ-19 ወረርሽኝን ጨምሮ ብዙ ታሪካዊ ክስተቶችን፣ ምንም እንኳን እነዚህን ክስተቶች በስም ባይጠቅሳቸውም እንደተነበየ ይናገራሉ።

ማክሰኞ 3 ፌብሩዋሪ 2026 ጥዋት 4:03:04
የጄፍሪ ኤፕስቲን ሰነዶች ይፋ መሆናቸውን ተከትሎ በመላው ዓለም የሚገኙ ታዋቂ ግለሰቦች እና ተቋማት በአሉታዊ መልኩ ስማቸው እየተነሳ ነው። በዚህም ምክንያት ፖለቲከኞች እና ታዋቂ ሰዎች ዝናቸው ጥያቄ ውስጥ ገብቶ አንዳንዶቹም ከሥልጣን እና ከኃላፊነታቸው እየለቀቁ ነው። ለመሆኑ ለዚህ ሁሉ ቀውስ ምክንያት የሆነው ጄፍሪ ኤፕስቲን ማን ነው?

ሐሙስ 5 ማርች 2026 ጥዋት 4:05:05
በአውሮፓውያኑ ጥር 25/1995 ኖርዌይ ‘ኖርዘርን ላይትስ’ የተባለውን የሰማይ ላይ ደማቅ ብርሃን ለማጥናት የተኮሰችውን ሮኬት ሩሲያ በስህተት ወደ ሞስኮ የተወነጨፈ የኒውክሌር ሚሳዔል እንደሆነ ቆጥራው ነበር። ከቀዝቃዛ ጦርነት ስሜት ገና በቅጡ ያላገገመው ዓለም በአንድ የአዘቦት ቀን ለሰዓታት የቆየ በድጋሚ ጦርነት ውስጥ የመግባት አስከፊ ስጋት ተጋርጦባት ነበር።

እሑድ 1 ፌብሩዋሪ 2026 ጥዋት 4:39:15
የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ ሳይንስ እና ባህል ተቋም በዓለም የማይዳሰሱ ቅርሶች ዝርዝር ውስጥ ኩልን አካቶታል።

ዓርብ 27 ፌብሩዋሪ 2026 ጥዋት 4:11:37
ለእስልምና እና ለክርስትና እመነት ተከታዮች ዋነኞቹ የፆም ወቅት የሆኑት ረመዳን እና ዓቢይ ፆሞች ተጀምረዋል። የሁለቱም እምነቶነቶች ምዕመናን የፆሙን ጊዜ በየራሳቸው ሥርዓት እና ደንብ መሠረት የሚከውኑት ሲሆን፣ በየዕለቱ ለረጅም ሰዓታት ከምግብ እና ከውሃ ርቀው ይቆያሉ። በዚህ ጊዜ ታዲያ ፆም በሰውነት ላይ ምን ለውጥን ያስከትላል? ምንስ ጥቅም አለው?

ሐሙስ 12 ፌብሩዋሪ 2026 ጥዋት 3:59:24
አቶ ነብዩ ማኅበራዊ ሚዲያ በታዳጊ ልጆች ላይ የሚያስከትለውን ተጽእኖ በተመለከተ መራራ የሆነ ልምድ ነው ያላቸው። የ13 ዓመቷ ልጃቸው ፊዮሬላ ላይ ምንም ዓይነት ምልክት ሳይመለከቱ በእኩዮቿ ጫና እና በማኅበራዊ ሚዲያ ግፊት ባላሰቡት ጊዜ ልጃቸው እራሷን አጥፍታ አግኝተዋታል።

ማክሰኞ 10 ፌብሩዋሪ 2026 ጥዋት 3:56:00

ሰኞ 8 ዲሴምበር 2025 ጥዋት 4:00:16
ከሌሊት ወፎች የሚነሳው የማርበርግ ቫይረስ ለመጀመሪያ ጊዜ ኢትዮጵያ ውስጥ ከተገኘ አንድ ወር ሊደፍን ጥቂት ቀናት ቀርተውታል። የጤና ሚኒስቴር፤ እንዴት በሽታው በጂንካ ከተማ ሊነሳ እንደቻለ እስካሁን አልገለጸም። ለመሆኑ በጂንካ የመጀመሪያው ታማሚ ማን ነበር? የበሽታው መነሻ የሆኑት የሌሊት ወፎችን እና የመጀመሪያውን ታማሚስ ምን አገናኛቸው? ቢቢሲ ባደረጋቸው በርካታ ቃለ መጠይቆች ለእነዚህ ጥያቄዎች መልስ የሚሆኑ መረጃዎች አሰባስቧል።

ረቡዕ 19 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 4:01:04
ከሁለት ዓመት በላይ የሆነው በአማራ ክልል በመንግሥት ኃይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል በሚካሄደው ግጭት ሰላማዊ ሰዎች ከባድ ዋጋ እየከፈሉ ነው። ግጭቱ በሰው ሕይወት እና በንብረት ላይ ከሚያደርሰው ጉዳት ባሻገር በሴቶች ላይ የሚፈጸመው ጥቃት እና ሰቆቃ ትኩረትን አላገኘም። ቢቢሲ ለወራት ባካሄደው ክትትል ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሴቶች የመደፈር እና የወሲባዊ ጥቃት ሰለባ መሆናቸውን መረጃ አግኝቷል።

ቅዳሜ 1 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 4:53:34
ሰሞኑን አረቄ ብሔራዊ አጀንዳ ሆና የማኅበራዊ ሚዲያ አናት ላይ ወጥታ ነበር። ጠጅ ቢሆን አናት ላይ አይወጣም፤ ወደ ጉልበት ነው የሚወርደው። ጠጅ ለመጨረሻ ጊዜ ጉዳይ ሆኖ የሥነ መንግሥቱ አናት ላይ ወጥቶ፣ ‘ብሔራዊ አጀንዳ’ የነበረው በዐፄ ዮሐንስ 4ኛ ዘመን ነው። ድሮ ጠጅ በብርሌ ይቀርብ ነበር። ከዚያ በብርሌ ይጠጣ ጀመር። ጠጅ ግን እንደ አረቄ ማንም ‘ተራ ዜጋ’ ብድግ አድርጎ አያንደቀድቀውም።ብርሌ ውስጥ የመደብ ታሪክ አለ። የዘመን ታሪክ አለ። የጭሰኛና የመሳፍንት ታሪክ አለ። ያልተሳከረ።

ቅዳሜ 22 ፌብሩዋሪ 2025 ጥዋት 4:53:16
ከተከፈተ በዚህ ወር 20 ዓመት የሆነው የቪዲዮ ማጋሪያው የማኅበራዊ ሚዲያ መድረክ ዩቲዩብ ለብዙዎች የተለያዩ አጋጣሚዎችን ፈጥሯል። ከእነዚህም መካከል አቤል ብርሃኑ አንዱ ነው፤ በዩቲዩብ አማካኝነት 62 ሀገራትን ዟሯል። ያልረገጠው አህጉር አንታርቲካን ብቻ ነው። ሁሉንም የአሜሪካ ግዛቶች አካሏል። ከዘጠኝ ዓመታት በላይ ዩቲዩብ ላይ የቆየው አቤል ከዩቲዩብ ምንያህል ያገኛል?

ዓርብ 24 ሜይ 2024 ጥዋት 4:16:17
ከእንግሊዝ ታላላቅ ቡድኖች መካከል አንዱ የሆነው የአርሰናል የልብ ደጋፊ የሆኑት ወ/ሮ እቴቱ ማሞ የ65 ዓመት እናት ናቸው። ላለፉት 20 ዓመታት አርሰናልን ያለማቋረጥ ደግፈዋል። እንደብዙዎቹ የቡድኑ ደጋፊዎች ዘንድሮ አርሰናል ዋንጫ ባለማንሳቱ ቢከፉም ድጋፋቸው ግን እንደሚቀጥል ይናገራሉ። ከሁሉም ተጫዋቾች ይልቅ እሳቸው ገብረኢየሱ ለሚሉት ለጋብሬል ጀሱስ እና ለቡካዮ ሳካ የተለየ ፍቅር አላቸው።

ረቡዕ 4 ጁን 2025 ጥዋት 4:00:19
ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ውስጥ በሕዝብ እና በጭነት ተሽከርካሪዎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች እና እገታዎች ተበራክተዋል። ይህ ክስተት ደግሞ ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት ላይ በሚገኘው የሰሜን ሸዋ አካባቢ በተደጋጋሚ ሲከሰት ቆይቷል። በተለይ አሊ ዶሮ የሚባለው ቦታ የጥቃት እና የእገታ ማዕከል ሆኗል እየተባለ ነው። ቢቢሲ በተለይ ይህ ቦታ ለምን የመንገደኞች እና የአሽከርካሪዎች ‘የሞት ቀጣና’ ሆነ? በሚል ለወራት የዘለቀ ምርመራ አድርጓል።

ሰኞ 18 ኖቬምበር 2024 ጥዋት 3:53:07
ግንቦት 2015 ዓ.ም. የተፈጸመው የፀጋ በላቸው ጠለፋ ብዙዎችን ያስቆጣ፣ መነጋገሪያም የሆነ የወንጀል ድርጊት ነበር። ፀጋ፤ ከአንድ ዓመት ከመንፈቅ በፊት ተጠልፋ ያሳለፈቻቸውን ቀናት በተመለከተ ለመጀመሪያ ጊዜ ለቢቢሲ በዝርዝር ተናግራለች። ከቢቢሲ ጋር በነበራት ዘለግ ያለ ቆይታ፤ ስለተጠለፈችበት መንገድ እና ስላሳለፈቻቸው ዘጠኝ ቀናት በዝርዝር ተርካለች። ከጠለፋው ነጻ የወጣችበት መንገድም አስቀድሞ በክልሉ መንግሥት ከተገለጸው የተለየ እንደሆነ ለመጀመሪያ ጊዜ ተናግራለች። ለምን ከኢትዮጵያ እንደተሰደደች እና ስለ ቀጣይ ዕቅዶቿም እንዲሁ አጋርታለች።

ሰኞ 12 ሜይ 2025 ጥዋት 4:02:02
ባለፉት ዓመታት በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች ውስጥ የሚካሄዱ ግጭቶች እና በታጣቂዎች የሚፈጸሙ እገታዎች ዜጎች በፈለጉት ጊዜ እና መንገድ በአገሪቱ ውስጥ እንዳይንቀሳቀሱ ብርቱ ስጋት ፈጥሮባቸዋል። በተለይ ደግሞ የመንገደኞች ማጓጓዣ ተሽከርካሪዎችን በማድረግ የሚፈጸሙት ያላባሩ እገታዎች በዋነኞቹ የአገሪቱ ክልሎች ውስጥ እንቅስቃሴን አዳጋች አድርገውታል። በዚህም ሳቢያ አቅሙ ያላቸው እና የግድ የሆነባቸው ሰዎች ፊታዎችን ወደ አየር ትራንስፖርት አዙረዋል።

ዓርብ 7 ማርች 2025 ጥዋት 3:50:04
ፓላንዳዊቷ ዶ/ር ኤቫን የአማርኛ ቋንቋን ከ40 ዓመት በፊት ተምራ በዲግሪ ከተመረቀች በኋላ ከሃያ ዓመታት በላይ በማስተማር በርካቶችን በአማርኛ ቋንቋ ዲግሪ አስይዛለች። የምታስተምርበት ዩኒቨርስቲ ወደ 80 ዓመታት ለሚጠጋ ጊዜ አማርኛን እያስተማረ ነው። አማርኛ ቋንቋን “ፏፏቴ ነው” የምትለው ዶ/ር ኤቫን በአገሯ በአማርኛ አስተርጓሚነት ትሠራለች። ለመሆኑ እንዴት ከአማርኛ ጋር ተዋወቀች?

ሐሙስ 19 ዲሴምበር 2024 ጥዋት 4:54:19
በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ጉልህ ስፍራ ካላቸው ፖለቲከኞች መካከል ጃዋር መሃመድ አንዱ ነው። ለዓመታት ያህል በኦሮሚያ የነበሩ ትግሎችን እንዲሁም ተቃውሞዎችን ከጀርባም ሆነ ከፊት ሆኖ በማስተባበር እና በመምራት ግንባር ቀደም ነው።የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ፓርቲ አመራሩ ጃዋር ከትውልድ አንስቶ በፖለቲካ ህይወቱ የተጓዘበትን ህይወቱ ላይ የሚያጠነጥን ‘አልጸጸትም’ የተሰኘውን መጽሐፍ ታህሳስ 10/ 2017 ዓ.ም በኬንያዋ መዲና ናይሮቢ ያስመርቃል። ጃዋር መሃመድ በአገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ፣ በቀጣይ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ስለሚኖረው ሚና፣ አገሪቱ ስላለችበት ሁኔታ ከቢቢሲ አማርኛ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ሰኞ 30 ሴፕቴምበር 2024 ጥዋት 4:13:42
ይህ ጥናታዊ ዘገባ የዩኒቨርስቲ መምህራን ላይ ያጠነጥናል፤ ከእነርሱም ውስጥ ፒኤችዲ (ዶክትሬት) የሚማሩት ላይ ያተኩራል። መምህራኑ የበለጠ በተማሩ ቁጥር የበለጠ እየተራቡ እንደሆነ ያወሳሉ። ቢቢሲ በርከት ያሉ የፒኤችዲ ተማሪዎችን ለወራት ቃለ መጠይቅ ሲያደርግ ቆይቷል። ከጉዳዩ ስፋት የተነሳ የብዙዎቹ አስቸጋሪ የኑሮ ሁኔታ እና ታሪክን በሚወክሉ በአምስት መምህራን ተወክሎ ቀርቧል።

ሰኞ 17 ማርች 2025 ጥዋት 3:41:37
“የብዙ ኢትዮጵያዊ ደም ነው የወሰደው። የኢትዮጵያ ደም ነው ያለህ እንለዋለን” ይህ በሶማሊያ የኢትዮጵያ የቀድሞ አምባሳደር ወንድሙ አሳምነው ለአሁኑ የጁባላንድ ግዛት ፕሬዚዳንት ማዶቤ በቀልድ መልኩ ጣል ያደርጉላቸው ነገር ነው። ይህ በቀልድ የተለወሰ መሪር እውነታ ነው። እውነታው የሶማሊያዋን ራስ ገዝ ጁባላንድን ላለፉት 12 ዓመታት ያስተዳደረው ማዶቤ በአንድ ወቅት በኢትዮጵያ ጦር ክፉኛ ቆስሎ በአዲስ አበባ ህክምና አድርጓል።

ቅዳሜ 19 ኤፕሪል 2025 ጥዋት 4:57:24
ወታደራዊው አስተዳደር ደርግ የአገሪቱን የመሪነት መንበር ከያዘ በኋላ የዛሬ 50 ዓመት የዕድገት በኅብረት ዘመቻን አወጀ። በዚህም ከ10ኛ ክፍል እስከ ዩኒቨርስቲ ያሉ ተማሪዎች እና መምህራን በገጠሪቱ ኢትዮጵያ ተሰማርተው በማስተማር እና በልማት ሥራዎች ላይ እንዲሳተፉ አድርጎ ነበር። በዚህ ዘመቻ የተሳተፉ የዚያ ዘመን አፍላ ወጣቶች ከአምስት አሥርታት በኋላ በጋራ ተሰባስበው ያሳለፉትን ጊዜ አስታውሰዋል። ትዝታቸውንም ለቢቢሲ አጋርተዋል. . .