
ሰኞ 16 ፌብሩዋሪ 2026 ጥዋት 3:55:06
ፕሬዝዳንቷ ለይፋዊ ጉብኝት በዚህ ሳምንት ወደ ኢትዮጵያ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የሚያቀኑት ቱርክ በወሳኝ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ተሰሚነቷ እየጎላ ነው። አገሪቱ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በተለያዩ አገራት መካከል ባጋጠሙ ቀውሶች ውስጥ በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ ትነሳለች። ለመሆኑ ቱርክ ጉልህ ሚና በነበራት ጉዳዮች ውስጥ ምን አሳካች? ምንስ እንቅፋት ገጠማት?

__
የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ በዩናይትድ ስቴትስ እና በኢራን መካከል የሚደረስ ማንኛውም ስምምነት ሁሉንም የበለፀገውን ዩራኒየም ከኢራን ማስወገድ እና ቴህራን ከዚህ በኋላ እንዳታበለጽግ ማድረግ አለበት አሉ።

እሑድ 15 ፌብሩዋሪ 2026 ጥዋት 4:55:55
በመቶዎች ከሚቆጠሩ ዓመታት በኋላ ደጋፊዎቹ ሁለቱንም የዓለም ጦርነቶች፣ የሂሮሺማ እና የናጋሳኪ የኒውክሌር ፍንዳታዎችን፣ የሂትለርን መነሳት እና የኮቪድ-19 ወረርሽኝን ጨምሮ ብዙ ታሪካዊ ክስተቶችን፣ ምንም እንኳን እነዚህን ክስተቶች በስም ባይጠቅሳቸውም እንደተነበየ ይናገራሉ።

ሐሙስ 12 ፌብሩዋሪ 2026 ጥዋት 3:59:24
አቶ ነብዩ ማኅበራዊ ሚዲያ በታዳጊ ልጆች ላይ የሚያስከትለውን ተጽእኖ በተመለከተ መራራ የሆነ ልምድ ነው ያላቸው። የ13 ዓመቷ ልጃቸው ፊዮሬላ ላይ ምንም ዓይነት ምልክት ሳይመለከቱ በእኩዮቿ ጫና እና በማኅበራዊ ሚዲያ ግፊት ባላሰቡት ጊዜ ልጃቸው እራሷን አጥፍታ አግኝተዋታል።

ዓርብ 13 ፌብሩዋሪ 2026 ጥዋት 4:01:01
በአማራ ክልል የደቡብ ጎንደር ዞን መቀመጫ በሆነችው ደብረ ታቦር ከተማ በፋኖ ታጣቂዎች እና በመንግሥት ኃይሎች መካከል በተካሄደ ግጭት የሕይወት እና የንብረት ጉዳት መድረሱን ነዋሪዎች ተናገሩ። የከተማዋ አስተዳደር ባወጣው መግለጫ ታጣቂዎች በመንግሥት እና በግለሰብ ንብረት ላይ ውድመት እና ዘረፋ መፈፀማቸውን አመልክቷል።

እሑድ 8 ፌብሩዋሪ 2026 ከሰዓት 12:34:49
የኤርትራ ሠራዊት ተቆጣጣሯቸዋል ካላቸው የኢትዮጵያ ሉዓላዊ ግዛቶች እንዲወጣ እና ለድርድር ዝግጁ እንዲሆን የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጠየቀ። ሚኒስቴሩ ቅዳሜ ጥር 30/2018 ዓ.ም. ለኤርትራው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በጻፈው ደብዳቤ ላይ ኤርትራ የኢትዮጵያን ሉዓላዊ ድንበር በመጣስ በሰሜን ምሥራቅ አቅጣጫ የሚገኙ አካባቢዎችን ተቆጣጥራ እንደምትገኝ ገልጿል።

ሰኞ 9 ፌብሩዋሪ 2026 ጥዋት 10:05:51
ኤርትራ የኢትዮጵያ ያቀረበችባትን ክስ “ትርጉም የለሽ” በማለት በዚህ ውዝግብ ውስጥ ለመግባት ፍላጎት እንደሌላት በማስታወቂያ ሚኒስቴሯ በኩል ባወጣችው አጭር መግለጫ አስታወቀች። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ኤርትራ ወደ ኢትዮጵያ ግዛት በመግባት የተወሰኑ አካባቢዎችን ተቆጣጥራለች እንዲሁም ታጣቂዎችን ትደግፋለች ሲል ቅዳሜ ዕለት በጻፈው ደብዳቤ ክስ እና የድርድር ጥያቄ አቅርቦ ነበር።

ዓርብ 6 ፌብሩዋሪ 2026 ከሰዓት 1:45:05
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በትግራይ ጦርነት ወቅት የኤርትራ ሠራዊት የሚፈጽማቸውን ግፎች እንዲያቆም የሚጠይቅ መልዕክት ወደ አሥመራ እንደላኩ የገለጹበትን የፓርላማ ንግግር የቀድሞው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገዱ አንዳርጋቸው አስተባበሉ። በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የተሠራጨው ባለሦስት ገጽ ደብዳቤም የራሳቸው መሆኑን ለቢቢሲ አረጋግጠዋል።

ረቡዕ 4 ፌብሩዋሪ 2026 ጥዋት 3:54:04
የትግራይ ክልል ዋና ከተማ መቀለን ጨምሮ በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች ከፍተኛ የነዳጅ አቅርቦት እጥረት ካጋጠመ ወራት መቆጠራቸውን ባለሥልጣናት እና የነዳጅ ማደያዎች ይናገራሉ። ነገር ግን ነዳጅ ከእጥፍ በላይ በሆነ ዋጋ በጥቁር ገበያ እየተሸጠ ይገኛል። ይህ ነዳጅ ከየት ነው የሚመጣ? የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ነው።

ሐሙስ 5 ፌብሩዋሪ 2026 ጥዋት 4:03:34
በየመን ሰነዓ በርካታ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ እና ወንጌላውያን አማኞች ከሃያ ዓመታት በላይ ሲገለገሉባቸው የቆዩ ቤተ እምነቶችን በሁቲ ባለሥልጣናት ከታሸጉ አንድ ወር እንደሞላቸው የእምነቱ ተከታዮች ለቢቢሲ ተናገሩ።

ሐሙስ 5 ፌብሩዋሪ 2026 ከሰዓት 3:15:51
ጉምቱው የአቪየሽን አመራር አቶ ግርማ ዋቄ የኡጋንዳ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተሹመዋል መባሉን የኡጋንዳ ፕሬዝዳንታዊ ጽህፈት ቤት አስተባበለ። ባለፈው ሳምንት የኡጋንዳ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጀኒፈር ባሙቱራቺ ከኃላፊነታቸው መነሳታቸውን ተከትሎ በኡጋንዳውያን የማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ዘንድ የአቶ ግርማ ዋቄ ስም በተተኪነት ሲነሳ ሰንብቷል።

ማክሰኞ 3 ፌብሩዋሪ 2026 ጥዋት 10:02:57
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ወቅት ትግራይ ውስጥ በኤርትራ ወታደሮች የተለያዩ ጥፋቶች መፈጸማቸውን እና በአገራቱ መካከል አሁን ለተባባሰው ችግር መነሻ መሆኑን ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥር 26/2018 ዓ.ም. ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽ በሰጡበት ወቅት በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ወቅት በኤትርትራ ወታደሮች ተፈጸሙ ስላሏቸው ውድመቶች ተናግረዋል።

ረቡዕ 4 ፌብሩዋሪ 2026 ጥዋት 7:01:02
የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገብረመስቀል፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስለ ኤርትራ መንግሥት ያደረጉት ንግግር፤ የኢትዮጵያ መንግሥት “በኤርትራ ላይ ሊከፍት ያቀደውን የጦርነት አጀንዳ ምክንያታዊ ለማድረግ” የቀረበ ነው ሲሉ ተቹ።

ማክሰኞ 3 ፌብሩዋሪ 2026 ጥዋት 4:03:04
የጄፍሪ ኤፕስቲን ሰነዶች ይፋ መሆናቸውን ተከትሎ በመላው ዓለም የሚገኙ ታዋቂ ግለሰቦች እና ተቋማት በአሉታዊ መልኩ ስማቸው እየተነሳ ነው። በዚህም ምክንያት ፖለቲከኞች እና ታዋቂ ሰዎች ዝናቸው ጥያቄ ውስጥ ገብቶ አንዳንዶቹም ከሥልጣን እና ከኃላፊነታቸው እየለቀቁ ነው። ለመሆኑ ለዚህ ሁሉ ቀውስ ምክንያት የሆነው ጄፍሪ ኤፕስቲን ማን ነው?

ረቡዕ 28 ጃንዋሪ 2026 ጥዋት 3:56:44
የኢትዮጵያ አየር ኃይል የተመሠረተበትን 90ኛ ዓመት ሲያከብር ያሉት የጦር አውሮፕላኖች እና ሌሎች ወታደራዊ በራሪዎች ትርዒት አቅርበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይም አየር ኃይሉ በወቅቱ እና በመጪው ዘመን ቴክኖሎጂዎች እየዘመነ መሆኑን ተናግረዋል። የአገራትን ወታደራዊ አቅም ደረጃን የሚያወጣው ግሎባል ፋየር ፓወር መረጃን መሠረት በማድረግ የኢትዮጵያን የአየር ኃይል ከጎረቤቶቿ ጋር ሲነጻጸር በምን ደረጃ ላይ ይገኛል?

እሑድ 8 ፌብሩዋሪ 2026 ጥዋት 5:05:47
ከ30 በላይ ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን በሊቢያ በአይኤስአይኤስ ከተገደሉ 11 ዓመት ሆኖታል። ያንን አሰቃቂ ግድያ ተዓምር በሚመስል መልኩ የተረፈው ዳንኤል አብርሃ ከአዲስ አበባ -ሊቢያ ከዚያም ዩናይትድ ኪንግደም ያለፈበትን ሁኔታ ስለሚተርክበት መጽሐፉ ከቢቢሲ ጋር ቆይታ አድርጓል።

እሑድ 1 ፌብሩዋሪ 2026 ጥዋት 4:39:15
የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ ሳይንስ እና ባህል ተቋም በዓለም የማይዳሰሱ ቅርሶች ዝርዝር ውስጥ ኩልን አካቶታል።

ዓርብ 26 ዲሴምበር 2025 ጥዋት 4:02:06
ስኪዞፍሪኒያ የሚባል የአእምሮ ጤና መታወክ እንዴት ያለ ነው? ፕሮፌሰር ሰለሞን ተፈራ ፒኤችዲ ሠርተውበታል። ለ20 ዓመት ተመራምረውበታል። በስኪዞፍሬኒያ የሚሰቃዩ በርካታ ታካሚዎች ነበሯቸው፤ አሏቸው። ፕሮፌሰሩ ነገርን በአጭር የማስረዳት ፀጋ አላቸው። ይህን የአእምሮ በሽታ እንዲህ ይገልጹታል። “ነገሩ የማርያምን ብቅል ሲፈጩ መዋል ነው” ይሉታል። ምን ማለታቸው ነው?

ዓርብ 19 ዲሴምበር 2025 ጥዋት 4:01:51
አይኤስ በመካከለኛው ምሥራቅ የነበረውን ድጋፍ እያጣ ከመጣ ወዲህ በአፍሪካ የተለያዩ አገራት ውስጥ እግሩን እያስገባ ነው። በምዕራብ አፍሪካ አገራት 12ሺህ የሚደርሱ ተዋጊዎች ያሉት አይኤስ በጎረቤት አገር ሶማሊያ ውስጥም ይንቀሳቀሳል። በዴሞክራቲክ ኮንጎ፣ በሞዛምቢክ እና ናይጄሪያም ቡድኑ እንቅስቃሴዎችን ያደርጋል።

ማክሰኞ 16 ዲሴምበር 2025 ጥዋት 3:50:26
ከከተፎካካሪዎቿ ዘግይታ ወደ ቀይ ባሕር ወታደራዊ ኃይሏን ለማስፈር የተቃረበችው ሩሲያ በወሳኙ የባሕር መተላለፊያ ላይ ላይ አዲስ ኃይል ትሆናለች። በአፍሪካ የመጀመሪያዋን የባሕር ኃይል ጦር ሰፈር ለመመሥረት ስትጥር የቆየችው ሩሲያ አሁን ፍላጎቷን ዕውን ለማድረግ ተቃርባለች። ይህ የሩሲያ ኃይል ወደ ቀጣናው መምጣት ምን ይዞ ይመጣል?

ሰኞ 10 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 8:03:16
አዲሱ የሶሪያ ፕሬዝዳንት አህመድ አል ሻራ በአግባቡ የተተኮሰ ሱፍ ለብሰው፣ ፀጉራቸውን ወደ ኋላ አበጥረው ወደ ዓለም አቀፍ መድረክ ሲመጡ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ እንዳሉ ያስታውቃል። አሁን የትግል ልብሳቸውን ትተው፣ አዲስ ስም ይዘው በዓለም ላይ ካሉት በጣም ኃያላን መሪዎች ጋር ይጨባበጣሉ።

ማክሰኞ 14 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 3:57:07
በመካከለኛው ምሥራቅ ኃያል እና ብቸኛዋ የአይሁዶች አገር የሆነችው እስራኤል በዙሪያዋ ካሉ አገራት ሁሉ በዕድሜ ትንሿ ናት። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ማብቃት በኋላ በአውሮፓውያኑ 1948 የእስራኤል እንደ አገር መመሥረት በአካባቢው አሁን ድረስ እየተካሄደ ያለ ለውጥን አስከትሏል። ለመሆኑ በየዕለቱ የዓለም መገናኛ ብዙኃን ስሟን ሳያነሱ የማያልፏት ይህች አገር እንዴት ተመሠረተች?

ቅዳሜ 13 ሴፕቴምበር 2025 ጥዋት 4:56:17
በኳታር ዋና ከተማ ዶሃ ውስጥ እስራኤል ጥቃት የፈጸመችው በርካታ የሐማስ ፖለቲካ ቢሮ ባለሥልጣናት በሚኖሩበት የመኖሪያ አካባቢ ላይ ነው። በዚህ ጥቃት አስከ ስምንት የሚደርሱ ፍንዳታዎችን እና ከፍተኛ ጭስ በዶሃ ሰሜናዊ ክፍል ላይ ማየታቸውን ዓይን እማኞች ተናግረዋል። ከጥቃቱ ደቂቃዎች በኋላ ደግሞ እስራኤል ለተፈጸመው ጥቃት በይፋ ኃላፊነቱን ወስዳለች።

ረቡዕ 20 ኦገስት 2025 ጥዋት 3:56:27
የጠቅላይ ሚኒስትር ዴቪድ ቤን ጉርዮን መንግሥት በዓለም ታዋቂ የሆነው ሳይንቲስት አልበርት አንስታይን ለእስራኤል ፕሬዝዳንትነት እንዲሆን ካጩት በኋላ በዩናይትድ ስቴትስ የእስራኤል አምባሳደር አባ ኢባን አንስታይንን እንዲያነጋግሩ ተደረገ።

ሰኞ 11 ኦገስት 2025 ጥዋት 4:01:11
ሁለት ዓመት ሊሞላው በተቃረበው ጦርነት በጋዛ ሰርጥ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ሲገደሉ የግዛቲቱ አብዛኛው ክፍል ፈራርሷል። እስራኤል ዘመቻዋን ስትጀምር ያስቀመጠቻቸው ታጋቾችን የማስለቀቅ እና ሐማስን የመደምሰስ ዕቅዷ ከግቡ አልደረሰም። ከወዳጆቿ ሳይቀር ተቃውሞ ቢገጥማትም አሁን ደግሞ ጋዛን ሙሉ ለሙሉ የመቆጣጠር ዕቅድ እንዳላት ይፋ አድርጋለች። በርካታ መሪዎቹ የተገደሉበት ሐማስ ከዚህ ጦርነት በኋላ ዕጣ ፈንታው ምን ሊሆን ይችላል?

ሐሙስ 12 ፌብሩዋሪ 2026 ጥዋት 3:59:24
አቶ ነብዩ ማኅበራዊ ሚዲያ በታዳጊ ልጆች ላይ የሚያስከትለውን ተጽእኖ በተመለከተ መራራ የሆነ ልምድ ነው ያላቸው። የ13 ዓመቷ ልጃቸው ፊዮሬላ ላይ ምንም ዓይነት ምልክት ሳይመለከቱ በእኩዮቿ ጫና እና በማኅበራዊ ሚዲያ ግፊት ባላሰቡት ጊዜ ልጃቸው እራሷን አጥፍታ አግኝተዋታል።

ማክሰኞ 10 ፌብሩዋሪ 2026 ጥዋት 3:56:00

ሰኞ 12 ጃንዋሪ 2026 ጥዋት 10:07:17
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ግዙፍ የሚባለው የአውሮፕላን ማረፊያ ከአዲስ አበባ 40 ኪሎ ሜትር ያህል በሚርቅ ቦታ ላይ ለመገንባት ሥራ ጀምራለች። ይህ አውሮፕላን ማረፊያ መሃል አዲስ አበባ ውስጥ ከሚገኘው በብዙ እጥፍ የሚበልጡ መንገደኞችን ያስተናግዳል ተብሏል። ይህንን ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያን ለምን አሁን መገንባት አስፈለገ? ቦታውስ ለምን ተመረጠ?

ሰኞ 8 ዲሴምበር 2025 ጥዋት 4:00:16
ከሌሊት ወፎች የሚነሳው የማርበርግ ቫይረስ ለመጀመሪያ ጊዜ ኢትዮጵያ ውስጥ ከተገኘ አንድ ወር ሊደፍን ጥቂት ቀናት ቀርተውታል። የጤና ሚኒስቴር፤ እንዴት በሽታው በጂንካ ከተማ ሊነሳ እንደቻለ እስካሁን አልገለጸም። ለመሆኑ በጂንካ የመጀመሪያው ታማሚ ማን ነበር? የበሽታው መነሻ የሆኑት የሌሊት ወፎችን እና የመጀመሪያውን ታማሚስ ምን አገናኛቸው? ቢቢሲ ባደረጋቸው በርካታ ቃለ መጠይቆች ለእነዚህ ጥያቄዎች መልስ የሚሆኑ መረጃዎች አሰባስቧል።

ረቡዕ 19 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 4:01:04
ከሁለት ዓመት በላይ የሆነው በአማራ ክልል በመንግሥት ኃይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል በሚካሄደው ግጭት ሰላማዊ ሰዎች ከባድ ዋጋ እየከፈሉ ነው። ግጭቱ በሰው ሕይወት እና በንብረት ላይ ከሚያደርሰው ጉዳት ባሻገር በሴቶች ላይ የሚፈጸመው ጥቃት እና ሰቆቃ ትኩረትን አላገኘም። ቢቢሲ ለወራት ባካሄደው ክትትል ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሴቶች የመደፈር እና የወሲባዊ ጥቃት ሰለባ መሆናቸውን መረጃ አግኝቷል።

ቅዳሜ 1 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 4:53:34
ሰሞኑን አረቄ ብሔራዊ አጀንዳ ሆና የማኅበራዊ ሚዲያ አናት ላይ ወጥታ ነበር። ጠጅ ቢሆን አናት ላይ አይወጣም፤ ወደ ጉልበት ነው የሚወርደው። ጠጅ ለመጨረሻ ጊዜ ጉዳይ ሆኖ የሥነ መንግሥቱ አናት ላይ ወጥቶ፣ ‘ብሔራዊ አጀንዳ’ የነበረው በዐፄ ዮሐንስ 4ኛ ዘመን ነው። ድሮ ጠጅ በብርሌ ይቀርብ ነበር። ከዚያ በብርሌ ይጠጣ ጀመር። ጠጅ ግን እንደ አረቄ ማንም ‘ተራ ዜጋ’ ብድግ አድርጎ አያንደቀድቀውም።ብርሌ ውስጥ የመደብ ታሪክ አለ። የዘመን ታሪክ አለ። የጭሰኛና የመሳፍንት ታሪክ አለ። ያልተሳከረ።

ቅዳሜ 22 ፌብሩዋሪ 2025 ጥዋት 4:53:16
ከተከፈተ በዚህ ወር 20 ዓመት የሆነው የቪዲዮ ማጋሪያው የማኅበራዊ ሚዲያ መድረክ ዩቲዩብ ለብዙዎች የተለያዩ አጋጣሚዎችን ፈጥሯል። ከእነዚህም መካከል አቤል ብርሃኑ አንዱ ነው፤ በዩቲዩብ አማካኝነት 62 ሀገራትን ዟሯል። ያልረገጠው አህጉር አንታርቲካን ብቻ ነው። ሁሉንም የአሜሪካ ግዛቶች አካሏል። ከዘጠኝ ዓመታት በላይ ዩቲዩብ ላይ የቆየው አቤል ከዩቲዩብ ምንያህል ያገኛል?

ዓርብ 24 ሜይ 2024 ጥዋት 4:16:17
ከእንግሊዝ ታላላቅ ቡድኖች መካከል አንዱ የሆነው የአርሰናል የልብ ደጋፊ የሆኑት ወ/ሮ እቴቱ ማሞ የ65 ዓመት እናት ናቸው። ላለፉት 20 ዓመታት አርሰናልን ያለማቋረጥ ደግፈዋል። እንደብዙዎቹ የቡድኑ ደጋፊዎች ዘንድሮ አርሰናል ዋንጫ ባለማንሳቱ ቢከፉም ድጋፋቸው ግን እንደሚቀጥል ይናገራሉ። ከሁሉም ተጫዋቾች ይልቅ እሳቸው ገብረኢየሱ ለሚሉት ለጋብሬል ጀሱስ እና ለቡካዮ ሳካ የተለየ ፍቅር አላቸው።

ረቡዕ 4 ጁን 2025 ጥዋት 4:00:19
ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ውስጥ በሕዝብ እና በጭነት ተሽከርካሪዎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች እና እገታዎች ተበራክተዋል። ይህ ክስተት ደግሞ ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት ላይ በሚገኘው የሰሜን ሸዋ አካባቢ በተደጋጋሚ ሲከሰት ቆይቷል። በተለይ አሊ ዶሮ የሚባለው ቦታ የጥቃት እና የእገታ ማዕከል ሆኗል እየተባለ ነው። ቢቢሲ በተለይ ይህ ቦታ ለምን የመንገደኞች እና የአሽከርካሪዎች ‘የሞት ቀጣና’ ሆነ? በሚል ለወራት የዘለቀ ምርመራ አድርጓል።

ሰኞ 18 ኖቬምበር 2024 ጥዋት 3:53:07
ግንቦት 2015 ዓ.ም. የተፈጸመው የፀጋ በላቸው ጠለፋ ብዙዎችን ያስቆጣ፣ መነጋገሪያም የሆነ የወንጀል ድርጊት ነበር። ፀጋ፤ ከአንድ ዓመት ከመንፈቅ በፊት ተጠልፋ ያሳለፈቻቸውን ቀናት በተመለከተ ለመጀመሪያ ጊዜ ለቢቢሲ በዝርዝር ተናግራለች። ከቢቢሲ ጋር በነበራት ዘለግ ያለ ቆይታ፤ ስለተጠለፈችበት መንገድ እና ስላሳለፈቻቸው ዘጠኝ ቀናት በዝርዝር ተርካለች። ከጠለፋው ነጻ የወጣችበት መንገድም አስቀድሞ በክልሉ መንግሥት ከተገለጸው የተለየ እንደሆነ ለመጀመሪያ ጊዜ ተናግራለች። ለምን ከኢትዮጵያ እንደተሰደደች እና ስለ ቀጣይ ዕቅዶቿም እንዲሁ አጋርታለች።

ሰኞ 12 ሜይ 2025 ጥዋት 4:02:02
ባለፉት ዓመታት በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች ውስጥ የሚካሄዱ ግጭቶች እና በታጣቂዎች የሚፈጸሙ እገታዎች ዜጎች በፈለጉት ጊዜ እና መንገድ በአገሪቱ ውስጥ እንዳይንቀሳቀሱ ብርቱ ስጋት ፈጥሮባቸዋል። በተለይ ደግሞ የመንገደኞች ማጓጓዣ ተሽከርካሪዎችን በማድረግ የሚፈጸሙት ያላባሩ እገታዎች በዋነኞቹ የአገሪቱ ክልሎች ውስጥ እንቅስቃሴን አዳጋች አድርገውታል። በዚህም ሳቢያ አቅሙ ያላቸው እና የግድ የሆነባቸው ሰዎች ፊታዎችን ወደ አየር ትራንስፖርት አዙረዋል።

ዓርብ 7 ማርች 2025 ጥዋት 3:50:04
ፓላንዳዊቷ ዶ/ር ኤቫን የአማርኛ ቋንቋን ከ40 ዓመት በፊት ተምራ በዲግሪ ከተመረቀች በኋላ ከሃያ ዓመታት በላይ በማስተማር በርካቶችን በአማርኛ ቋንቋ ዲግሪ አስይዛለች። የምታስተምርበት ዩኒቨርስቲ ወደ 80 ዓመታት ለሚጠጋ ጊዜ አማርኛን እያስተማረ ነው። አማርኛ ቋንቋን “ፏፏቴ ነው” የምትለው ዶ/ር ኤቫን በአገሯ በአማርኛ አስተርጓሚነት ትሠራለች። ለመሆኑ እንዴት ከአማርኛ ጋር ተዋወቀች?

ሐሙስ 19 ዲሴምበር 2024 ጥዋት 4:54:19
በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ጉልህ ስፍራ ካላቸው ፖለቲከኞች መካከል ጃዋር መሃመድ አንዱ ነው። ለዓመታት ያህል በኦሮሚያ የነበሩ ትግሎችን እንዲሁም ተቃውሞዎችን ከጀርባም ሆነ ከፊት ሆኖ በማስተባበር እና በመምራት ግንባር ቀደም ነው።የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ፓርቲ አመራሩ ጃዋር ከትውልድ አንስቶ በፖለቲካ ህይወቱ የተጓዘበትን ህይወቱ ላይ የሚያጠነጥን ‘አልጸጸትም’ የተሰኘውን መጽሐፍ ታህሳስ 10/ 2017 ዓ.ም በኬንያዋ መዲና ናይሮቢ ያስመርቃል። ጃዋር መሃመድ በአገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ፣ በቀጣይ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ስለሚኖረው ሚና፣ አገሪቱ ስላለችበት ሁኔታ ከቢቢሲ አማርኛ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ሰኞ 30 ሴፕቴምበር 2024 ጥዋት 4:13:42
ይህ ጥናታዊ ዘገባ የዩኒቨርስቲ መምህራን ላይ ያጠነጥናል፤ ከእነርሱም ውስጥ ፒኤችዲ (ዶክትሬት) የሚማሩት ላይ ያተኩራል። መምህራኑ የበለጠ በተማሩ ቁጥር የበለጠ እየተራቡ እንደሆነ ያወሳሉ። ቢቢሲ በርከት ያሉ የፒኤችዲ ተማሪዎችን ለወራት ቃለ መጠይቅ ሲያደርግ ቆይቷል። ከጉዳዩ ስፋት የተነሳ የብዙዎቹ አስቸጋሪ የኑሮ ሁኔታ እና ታሪክን በሚወክሉ በአምስት መምህራን ተወክሎ ቀርቧል።

ሰኞ 17 ማርች 2025 ጥዋት 3:41:37
“የብዙ ኢትዮጵያዊ ደም ነው የወሰደው። የኢትዮጵያ ደም ነው ያለህ እንለዋለን” ይህ በሶማሊያ የኢትዮጵያ የቀድሞ አምባሳደር ወንድሙ አሳምነው ለአሁኑ የጁባላንድ ግዛት ፕሬዚዳንት ማዶቤ በቀልድ መልኩ ጣል ያደርጉላቸው ነገር ነው። ይህ በቀልድ የተለወሰ መሪር እውነታ ነው። እውነታው የሶማሊያዋን ራስ ገዝ ጁባላንድን ላለፉት 12 ዓመታት ያስተዳደረው ማዶቤ በአንድ ወቅት በኢትዮጵያ ጦር ክፉኛ ቆስሎ በአዲስ አበባ ህክምና አድርጓል።

ቅዳሜ 19 ኤፕሪል 2025 ጥዋት 4:57:24
ወታደራዊው አስተዳደር ደርግ የአገሪቱን የመሪነት መንበር ከያዘ በኋላ የዛሬ 50 ዓመት የዕድገት በኅብረት ዘመቻን አወጀ። በዚህም ከ10ኛ ክፍል እስከ ዩኒቨርስቲ ያሉ ተማሪዎች እና መምህራን በገጠሪቱ ኢትዮጵያ ተሰማርተው በማስተማር እና በልማት ሥራዎች ላይ እንዲሳተፉ አድርጎ ነበር። በዚህ ዘመቻ የተሳተፉ የዚያ ዘመን አፍላ ወጣቶች ከአምስት አሥርታት በኋላ በጋራ ተሰባስበው ያሳለፉትን ጊዜ አስታውሰዋል። ትዝታቸውንም ለቢቢሲ አጋርተዋል. . .