
ሐሙስ 8 ጃንዋሪ 2026 ጥዋት 7:18:13
አሜሪካ ባለፈው ዓመት ለመጀመሪያ ጊዜ ተግባራዊ ያደረገችው ይህ አሰራር ቪዛ አመልካቾች እስከ 15 ሺህ ዶላር ድረስ ተያዥ እንዲያድርጉ ያትታል። በርካታ የአፍሪካ ሀገራት በዝርዝሩ ውስጥ የተካተቱ ሲሆን የትራምፕ አስተዳደር ይፋ ጠበቅ ያለ የቪዛ እርምጃ መውሰዱን ቀጥሏል። በዝርዝሩ ውስጥ የተካተቱ የአፍሪካ ሀገራት እነማን ናቸው? ተያዥ የሚደረገው ገንዘብስ ይመለሳል?

__
የአሜሪካ የኢሚግሬሽን መኮንን የ37 ዓመቷን እና የሦስት ልጆች እናት የሆነችውን አሜሪካዊት ተኩሶ መግደሉን ተከትሎ በሚኒያፖሊስ ተቃውሞ ተቀስቅሷል። የፌደራል ባለሥልጣናት ሟች ሬኔ ኒኮሌ ጉድ የኢምግሬሽን መኮንኑን ለማምለጥ ሙከራ አድርጋለች ብለው ሲከስሷት፣ የከተማዋ ከንቲባ ደግሞ ተኩሶ የገደላት ግለሰብ በግዴለሽነት እርምጃ ወስዷል ሲሉ ወንጅለውታል።

ረቡዕ 7 ጃንዋሪ 2026 ከሰዓት 1:24:48
የቡርኪና ፋሶ ወታደራዊ መሪ የሆኑትን ካፕቴይን ኢብራሂ ምትራኦሬን ለመግደል የተቀናበረ ሴራ መክሸፉን የምዕራብ አፍሪካዊቷ አገር መንግሥት አስታወቀ። የአገሪቱ የደኅንነት ሚኒስቴር እንደገለጸው መሪውን ለመግደል የረቀቀ የተባለ ሴራ የተቀናበረው ከሦስት ዓመት በፊት በትራኦሬ ከመሪነት በተገለበጡት ወታደራዊው መኮንን በሌተናንት ኮሎኔል ፖል ሄንሪ ዳሚባ ነው።

ማክሰኞ 6 ጃንዋሪ 2026 ጥዋት 4:08:03
በአሁኑ ጊዜ ጋምቤላ ክልል ለሳምንታት በዘለቀ አለመረጋጋት ውስጥ ናት። በክልሉ ውስጥ የሚከሰቱ ግጭቶች እና ጥቃቶች አዲስ ክስተቶች አይደሉም። ጋብ ብልጭ እያሉ የሚከሰቱት ብሔርን መሠረት ያደረጉ ግጭቶች የበርካቶችን ሕይወት እየቀጠፈ ለዓመታት ቆይቷል። ምንም እንኳን ክልሉን በተደጋጋሚ ግጭት ቢናጥም ዘላቂ መፍትሄ አልተገኘለትም። ለመሆኑ በየጊዜው እየተከሰተ ጋምቤላን ሰላም የሚነሳው ግጭት ምክንያቱ ምንድን ነው?

ሰኞ 29 ዲሴምበር 2025 ጥዋት 4:08:22
እስራኤል ለሶማሊላንድ የነጻ አገርነት ዕውቅናን መስጠቷን ተከትሎ ከየአቅጣጫው ተቃውሞ እየተሰማ ነው። ለሰላሳ ዓመታት በላይ እራሷን ከሶማሊያ ማዕከላዊ መንግሥት ለይታ የቆየችው ሶማሊላንድ የአገርነት ዕውቅናን ለማግኘት ያለፈችበት ሂደት ምን ይመስላል? የእስራኤል ውሳኔ በአፍሪካ ቀንድ እንዲሁም በአጠቃላዩ የኤደን ባሕረ ሰላጤ እና በቀይ ባሕር አካባቢ በሚኖረው ጂኦፖለቲካዊ አሰላለፍ እና ውጤቱ ላይ ምን ውጤት ይኖረዋል?

ማክሰኞ 30 ዲሴምበር 2025 ጥዋት 8:54:08
እንደ ቲክቶክ እና ዩቲዩብ ካሉ የማኅበራዊ ሚዲያ መድረኮች በዓመት ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ የሚያገኙ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች፤ እንቅስቃሴያቸው “በንግድ ሥራነት” ተቆጥሮ ግብር እንዲከፍሉ የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ ተዘጋጀ። የገንዘብ ሚኒስቴር ያዘጋጀው ረቂቅ ደንብ፤ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች “ማስታወቂያዎች እና ስፖንሰርሺፖችን” ጨምሮ በተለያዩ መንገዶች ያገኙትን “ሁሉንም የገቢ መጠን” የሚያሳይ “የሂሳብ መዝገብ” እንዲይዙ ያስገድዳል።

ረቡዕ 31 ዲሴምበር 2025 ጥዋት 10:26:21
በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ አያና ወረዳ “በኦሮሚያ ልዩ ኃይል” ተፈጽሟል በተባለ ጥቃት 19 ሰዎች ሲገደሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ቤቶች ደግሞ መቃጠላቸውን እና መዘረፋቸውን ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናገሩ። ተቃዋሚዎቹ እናት ፓርቲ እና ኢህአፓ ጥቃቱ “በመንግሥት መዋቅር የተፈጸመ” መሆኑን በመግለጽ ሲያወግዙት የክልሉ እና የአካባቢው ባለሥልጣናት አስካሁን ምንም ያሉት ነገር የለም።

ሐሙስ 25 ዲሴምበር 2025 ጥዋት 4:00:18
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ዩኤስኤአይዲን ካፈረሱ በኋላ አዲስ የእርዳታ እና የትብብር መረሃ ግብር አዘጋጅተው ከአገራት ጋር ስምምነት እየተፈራረሙ ነው። አዲሱ ዕቅድ የቀደመውን አሠራር በማስቀረት ከመንግሥታት ጋር የሚከናወን የጋራ የጤና ዘርፍ ትብብር ነው። ባለፉት ጥቂት ሳምንታት ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎችም አገራት እየፈረሙ ቢሆንም በተለይ ኬንያ ውስጥ በፍርድ ቤት ጊዜያዊ ዕግድ ተጥሎበታል። ይህ አዲስ መረሃ ግብር ምንድን ነው? ለምንስ አነጋጋሪ ሆነ?

ዓርብ 26 ዲሴምበር 2025 ከሰዓት 12:46:05
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ውስጥ በሚገኘው ቤሮ ወረዳ በትናንትናው ዕለት ታጣቂዎች በሦስት የወርቅ እና የእምነበረድ ማውጫ ስፍራዎች ላይ በፈጸሙ ጥቃቶች ሰባት ሰዎች መገደላቸውን የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ እና የፖሊስ አዛዥ ለቢቢሲ ተናገሩ። በዛሬው ዕለትም “በሌላ የማዕድን ስፍራ ላይ” የተኩስ ልውውጥ መደረጉን ተገልጿል።

ረቡዕ 24 ዲሴምበር 2025 ጥዋት 4:01:41
የገንዘብ ሚኒስቴር የንብረት ታክስ የሚጣልበትን እና የሚሰበሰብበትን መንገድ በተመለከተ ዝርዝር መረጃዎችን የያዘ “ሞዴል” ረቂቅ ሕግ በታኅሣሥ 2018 ዓ.ም. መጀመሪያ ወደ ክልል እና ከተማ አስተዳደሮች ልኳል። የንብረት ታክስን የመጣል እና የመሰብሰብ መብት የክልሎች ቢሆንም ከግብሩ ጋር ለሚያወጡት ሕግ “መነሻ የሚሆን ሞዴል” ረቂቅ ሕግ የሚዘጋጀው በፌደራል መንግሥት እንደሆነ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ደብዳቤ ያስረዳል።

ማክሰኞ 16 ዲሴምበር 2025 ጥዋት 9:34:01
የአሜሪካ መንግሥት ከሦስት ዓመት በፊት ኢትዮጵያውያን በጊዜያዊ የሕግ ጥበቃ በአገሪቱ ውስጥ እንዲኖሩ የፈቀደበትን አሠራር እንዲያከትም ወስኗል። ላለፉት ዓመታት ለኢትዮጵያውያን ጥገኝነት ጠያቂዎች ሲሰጥ የነበረው ይህ ጊዜያዊ የሕግ ጥበቃ በመነሳቱ ከለላው የነበራቸው ኢትዮጵያውያን በሁለት ወራት ከአሜሪካ መውጣት ይጠበቅባቸዋል። ለመሆኑ የኢትዮጵያዊያኑ ቀጣይ ዕጣ ፈንታ ምን ሊሆን ይችላል? ምንስ አማራጭ አላቸው?

ዓርብ 19 ዲሴምበር 2025 ጥዋት 4:01:51
አይኤስ በመካከለኛው ምሥራቅ የነበረውን ድጋፍ እያጣ ከመጣ ወዲህ በአፍሪካ የተለያዩ አገራት ውስጥ እግሩን እያስገባ ነው። በምዕራብ አፍሪካ አገራት 12ሺህ የሚደርሱ ተዋጊዎች ያሉት አይኤስ በጎረቤት አገር ሶማሊያ ውስጥም ይንቀሳቀሳል። በዴሞክራቲክ ኮንጎ፣ በሞዛምቢክ እና ናይጄሪያም ቡድኑ እንቅስቃሴዎችን ያደርጋል።

ዓርብ 26 ዲሴምበር 2025 ጥዋት 4:02:06
ስኪዞፍሪኒያ የሚባል የአእምሮ ጤና መታወክ እንዴት ያለ ነው? ፕሮፌሰር ሰለሞን ተፈራ ፒኤችዲ ሠርተውበታል። ለ20 ዓመት ተመራምረውበታል። በስኪዞፍሬኒያ የሚሰቃዩ በርካታ ታካሚዎች ነበሯቸው፤ አሏቸው። ፕሮፌሰሩ ነገርን በአጭር የማስረዳት ፀጋ አላቸው። ይህን የአእምሮ በሽታ እንዲህ ይገልጹታል። “ነገሩ የማርያምን ብቅል ሲፈጩ መዋል ነው” ይሉታል። ምን ማለታቸው ነው?

ሰኞ 8 ዲሴምበር 2025 ጥዋት 4:00:16
ከሌሊት ወፎች የሚነሳው የማርበርግ ቫይረስ ለመጀመሪያ ጊዜ ኢትዮጵያ ውስጥ ከተገኘ አንድ ወር ሊደፍን ጥቂት ቀናት ቀርተውታል። የጤና ሚኒስቴር፤ እንዴት በሽታው በጂንካ ከተማ ሊነሳ እንደቻለ እስካሁን አልገለጸም። ለመሆኑ በጂንካ የመጀመሪያው ታማሚ ማን ነበር? የበሽታው መነሻ የሆኑት የሌሊት ወፎችን እና የመጀመሪያውን ታማሚስ ምን አገናኛቸው? ቢቢሲ ባደረጋቸው በርካታ ቃለ መጠይቆች ለእነዚህ ጥያቄዎች መልስ የሚሆኑ መረጃዎች አሰባስቧል።

ሐሙስ 27 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 5:54:45
ሃይሊ ጉቢ እሳተ ገሞራ የፈነዳው ከ12ሺህ ዓመታት በኋላ ነው። እስከባለፈው እሑድ ድረስ አንዳችም እንቅስቃሴ ሳያሳይ ቆይቷል። የእሳተ ገሞራው አመድ በነፋስ አማካይነት አንድ ሺህ ጫማ ተጉዞ ጥቃቅን ቅንጣቶች ሰማይ ላይ ታይተዋል። ለመሆኑ ንቁ እሳተ ገሞራ እና ለዘብተኛ እሳተ ገሞራን ምን ይለያቸዋል? እሳተ ገሞራ ሊፈነዳ ሲል የሚያሳያቸው ምልክቶችስ የትኞቹ ናቸው?

ማክሰኞ 16 ዲሴምበር 2025 ጥዋት 3:50:26
ከከተፎካካሪዎቿ ዘግይታ ወደ ቀይ ባሕር ወታደራዊ ኃይሏን ለማስፈር የተቃረበችው ሩሲያ በወሳኙ የባሕር መተላለፊያ ላይ ላይ አዲስ ኃይል ትሆናለች። በአፍሪካ የመጀመሪያዋን የባሕር ኃይል ጦር ሰፈር ለመመሥረት ስትጥር የቆየችው ሩሲያ አሁን ፍላጎቷን ዕውን ለማድረግ ተቃርባለች። ይህ የሩሲያ ኃይል ወደ ቀጣናው መምጣት ምን ይዞ ይመጣል?

ሰኞ 10 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 8:03:16
አዲሱ የሶሪያ ፕሬዝዳንት አህመድ አል ሻራ በአግባቡ የተተኮሰ ሱፍ ለብሰው፣ ፀጉራቸውን ወደ ኋላ አበጥረው ወደ ዓለም አቀፍ መድረክ ሲመጡ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ እንዳሉ ያስታውቃል። አሁን የትግል ልብሳቸውን ትተው፣ አዲስ ስም ይዘው በዓለም ላይ ካሉት በጣም ኃያላን መሪዎች ጋር ይጨባበጣሉ።

ማክሰኞ 14 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 3:57:07
በመካከለኛው ምሥራቅ ኃያል እና ብቸኛዋ የአይሁዶች አገር የሆነችው እስራኤል በዙሪያዋ ካሉ አገራት ሁሉ በዕድሜ ትንሿ ናት። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ማብቃት በኋላ በአውሮፓውያኑ 1948 የእስራኤል እንደ አገር መመሥረት በአካባቢው አሁን ድረስ እየተካሄደ ያለ ለውጥን አስከትሏል። ለመሆኑ በየዕለቱ የዓለም መገናኛ ብዙኃን ስሟን ሳያነሱ የማያልፏት ይህች አገር እንዴት ተመሠረተች?

ቅዳሜ 13 ሴፕቴምበር 2025 ጥዋት 4:56:17
በኳታር ዋና ከተማ ዶሃ ውስጥ እስራኤል ጥቃት የፈጸመችው በርካታ የሐማስ ፖለቲካ ቢሮ ባለሥልጣናት በሚኖሩበት የመኖሪያ አካባቢ ላይ ነው። በዚህ ጥቃት አስከ ስምንት የሚደርሱ ፍንዳታዎችን እና ከፍተኛ ጭስ በዶሃ ሰሜናዊ ክፍል ላይ ማየታቸውን ዓይን እማኞች ተናግረዋል። ከጥቃቱ ደቂቃዎች በኋላ ደግሞ እስራኤል ለተፈጸመው ጥቃት በይፋ ኃላፊነቱን ወስዳለች።

ረቡዕ 20 ኦገስት 2025 ጥዋት 3:56:27
የጠቅላይ ሚኒስትር ዴቪድ ቤን ጉርዮን መንግሥት በዓለም ታዋቂ የሆነው ሳይንቲስት አልበርት አንስታይን ለእስራኤል ፕሬዝዳንትነት እንዲሆን ካጩት በኋላ በዩናይትድ ስቴትስ የእስራኤል አምባሳደር አባ ኢባን አንስታይንን እንዲያነጋግሩ ተደረገ።

ሰኞ 11 ኦገስት 2025 ጥዋት 4:01:11
ሁለት ዓመት ሊሞላው በተቃረበው ጦርነት በጋዛ ሰርጥ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ሲገደሉ የግዛቲቱ አብዛኛው ክፍል ፈራርሷል። እስራኤል ዘመቻዋን ስትጀምር ያስቀመጠቻቸው ታጋቾችን የማስለቀቅ እና ሐማስን የመደምሰስ ዕቅዷ ከግቡ አልደረሰም። ከወዳጆቿ ሳይቀር ተቃውሞ ቢገጥማትም አሁን ደግሞ ጋዛን ሙሉ ለሙሉ የመቆጣጠር ዕቅድ እንዳላት ይፋ አድርጋለች። በርካታ መሪዎቹ የተገደሉበት ሐማስ ከዚህ ጦርነት በኋላ ዕጣ ፈንታው ምን ሊሆን ይችላል?

ሰኞ 28 ጁላይ 2025 ጥዋት 7:47:12
ማሱድ ፔዜሽኪያን ሐምሌ 2024 የኢራን ፕሬዝዳንት ሆነው ከተሾሙ ከአንድ ቀን በኋላ በቀጥታ ወደ ፖለቲካ እሳት ውስጥ ገብተዋል። ይህም አለመረጋጋት በሌለው በኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ መሪዎች ታሪክ ውስጥ ከታዩት ጅማሪዎች መካከል እጅግ አስደንጋጩ እና በቀውስ የታጀበ ነበር።

ማክሰኞ 1 ጁላይ 2025 ጥዋት 3:57:49
በአውሮፓውያኑ መጋቢት 5/1957 ዩናይትድ ስቴትስ በወቅቱ በመሐመድ ሬዛ ፓህላቪ ከምትመራው ኢራን ጋር ለሲቪል የአውቶሚክ ኢነርጂ አጠቃቀም የትብብር ስምምነት ተፈራረመች። በ’አተምስ ፎር ፒስ’ መርሃ ግብር ጥላ ስር የነበረው ይህ ስምምነት የኢራንን የኒውክሌር መርሃ ግብር ለመጀመር መሠረት ጣለ። ለዋሽንግተን፣ በዚያ የቀዝቃዛ ጦርነት ወቅት ኢራን ተጨማሪ መስህብ ነበራት።

ሐሙስ 19 ጁን 2025 ጥዋት 3:52:56
እስራኤል ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ለአርብ አጥቢያ በፈጸመችው ጥቃት ቁልፍ የሚባሉ የኢራን የጦር አዛዦች እንዲሁም የኒውክሌር ሳይንቲስቶች መገደላቸው ያሉበትን ትክክለኛ ቦታ በተመለከተ መረጃ እንዳላት የሚያሳይ ነው። ከዚህ መረጃ እና ተልዕኮ ጀርባ ደግሞ የአገሪቱ የሥለላ ተቋም ሞሳድ እንዳለ ይታመናል። ሞሳድ ባለፉት ሰባት አስርት ዓመታት ውስጥ ከኢትዮጵያ እስከ ኢራን የፈጸማቸው ዋናዎቹ ተልዕኮዎች የትኞቹ ናቸው?

ሰኞ 23 ጁን 2025 ጥዋት 3:54:51
…የኢራን ከፍተኛ ጄነራሎች እሰራኤል ጥቃት ልትሰነዝር ትችላለች የሚለው ነገር አሳስቧቸው ስብሰባ ጠሩ። ሁልጊዜም እንደሚያደርጉት ‘የእስራኤል ነገር አይታወቅም’ ብለው ከመሬት ሥር በተዘጋጀ የምድር ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ ገቡ። ሞሳድ ግን ይህን ያውቅ ነበር። ቁልፍ ስብሰባዎች እዚህ ምድር ቤት እንደሚደረጉ መረጃ ነበረው።. . .

ዓርብ 13 ጁን 2025 ጥዋት 3:51:33
ኢራን እና እስራኤል ለረጅም ጊዜ በእጅ አዙር እንጂ በቀጥታ ግጭት ውስጥ ገብተው አየውቁም። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን አንደኛው በሌላኛው ላይ የቀጥታ ጥቃት እየፈጸሙ ከጦርነት አፋፍ ላይ መድረሳቸው አሳሳቢ ሆኗል። ለመሆኑ እስራኤል እና ኢራን ጦርነት ውስጥ ቢገቡ ምን ሊከሰት ይችላል? ሁለቱ አገራትስ በወታደራዊ አቅም ምን ያህል ይመጣጠናሉ?

እሑድ 15 ጁን 2025 ጥዋት 4:51:06
ኢራን ከግብፅ ቀጥላ ለእስራኤል እውቅና በመስጠት ሁለተኛዋ እስላማዊ አገር ነበረች። ነገር ግን ከኢራን እስላማዊ አብዮት በኋላ ይህ ግንኙነት ተበላሽቶ ከአራት አስርታት በላይ በጠላትነት እየተያዩ ቆይተዋል። ለመሆኑ የሁለቱ አገራት ግንኙነት ወደ ደመኛ ጠላትነት ለምን ተሸጋገረ?

ቅዳሜ 14 ጁን 2025 ጥዋት 4:31:37
እስራኤል በፈጸመችው ጥቃት በርካታ የአገሪቱ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዦች እና የኒውክሌር ሳይንቲስቶች መገደላቸውን ኢራን አረጋግጣለች። በጥቃቱ የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ የአየር ኃይል አዛዥን ጨምሮ ቢያንስ 20 የኢራን ወታደራዊ ኃይል ከፍተኛ አዛዦች ተገድለዋል። ይህ ኢራን የምትመካበት ወታደራዊ ኃይል ማን ነው? ምንስ አቅም አለው?

ዓርብ 26 ዲሴምበር 2025 ጥዋት 4:02:06
ስኪዞፍሪኒያ የሚባል የአእምሮ ጤና መታወክ እንዴት ያለ ነው? ፕሮፌሰር ሰለሞን ተፈራ ፒኤችዲ ሠርተውበታል። ለ20 ዓመት ተመራምረውበታል። በስኪዞፍሬኒያ የሚሰቃዩ በርካታ ታካሚዎች ነበሯቸው፤ አሏቸው። ፕሮፌሰሩ ነገርን በአጭር የማስረዳት ፀጋ አላቸው። ይህን የአእምሮ በሽታ እንዲህ ይገልጹታል። “ነገሩ የማርያምን ብቅል ሲፈጩ መዋል ነው” ይሉታል። ምን ማለታቸው ነው?

ዓርብ 5 ዲሴምበር 2025 ጥዋት 8:02:40
በዓለም አቀፍ ደረጃ የተደረጉ ጥናቶች እንደሚያሳዩት እስከ 58 በመቶ የሚሆኑ ሴቶች እና ልጃገረዶች በኦንላይን ለሚፈጸሙ ጥቃቶች ዒላማ መሆናቸውን የተባበሩት መንግሥታት የሴቶች ድርጅት አስታውቋል።

ረቡዕ 19 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 4:01:04
ከሁለት ዓመት በላይ የሆነው በአማራ ክልል በመንግሥት ኃይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል በሚካሄደው ግጭት ሰላማዊ ሰዎች ከባድ ዋጋ እየከፈሉ ነው። ግጭቱ በሰው ሕይወት እና በንብረት ላይ ከሚያደርሰው ጉዳት ባሻገር በሴቶች ላይ የሚፈጸመው ጥቃት እና ሰቆቃ ትኩረትን አላገኘም። ቢቢሲ ለወራት ባካሄደው ክትትል ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሴቶች የመደፈር እና የወሲባዊ ጥቃት ሰለባ መሆናቸውን መረጃ አግኝቷል።

ቅዳሜ 1 ኖቬምበር 2025 ጥዋት 4:53:34
ሰሞኑን አረቄ ብሔራዊ አጀንዳ ሆና የማኅበራዊ ሚዲያ አናት ላይ ወጥታ ነበር። ጠጅ ቢሆን አናት ላይ አይወጣም፤ ወደ ጉልበት ነው የሚወርደው። ጠጅ ለመጨረሻ ጊዜ ጉዳይ ሆኖ የሥነ መንግሥቱ አናት ላይ ወጥቶ፣ ‘ብሔራዊ አጀንዳ’ የነበረው በዐፄ ዮሐንስ 4ኛ ዘመን ነው። ድሮ ጠጅ በብርሌ ይቀርብ ነበር። ከዚያ በብርሌ ይጠጣ ጀመር። ጠጅ ግን እንደ አረቄ ማንም ‘ተራ ዜጋ’ ብድግ አድርጎ አያንደቀድቀውም።ብርሌ ውስጥ የመደብ ታሪክ አለ። የዘመን ታሪክ አለ። የጭሰኛና የመሳፍንት ታሪክ አለ። ያልተሳከረ።

ቅዳሜ 22 ፌብሩዋሪ 2025 ጥዋት 4:53:16
ከተከፈተ በዚህ ወር 20 ዓመት የሆነው የቪዲዮ ማጋሪያው የማኅበራዊ ሚዲያ መድረክ ዩቲዩብ ለብዙዎች የተለያዩ አጋጣሚዎችን ፈጥሯል። ከእነዚህም መካከል አቤል ብርሃኑ አንዱ ነው፤ በዩቲዩብ አማካኝነት 62 ሀገራትን ዟሯል። ያልረገጠው አህጉር አንታርቲካን ብቻ ነው። ሁሉንም የአሜሪካ ግዛቶች አካሏል። ከዘጠኝ ዓመታት በላይ ዩቲዩብ ላይ የቆየው አቤል ከዩቲዩብ ምንያህል ያገኛል?

ዓርብ 24 ሜይ 2024 ጥዋት 4:16:17
ከእንግሊዝ ታላላቅ ቡድኖች መካከል አንዱ የሆነው የአርሰናል የልብ ደጋፊ የሆኑት ወ/ሮ እቴቱ ማሞ የ65 ዓመት እናት ናቸው። ላለፉት 20 ዓመታት አርሰናልን ያለማቋረጥ ደግፈዋል። እንደብዙዎቹ የቡድኑ ደጋፊዎች ዘንድሮ አርሰናል ዋንጫ ባለማንሳቱ ቢከፉም ድጋፋቸው ግን እንደሚቀጥል ይናገራሉ። ከሁሉም ተጫዋቾች ይልቅ እሳቸው ገብረኢየሱ ለሚሉት ለጋብሬል ጀሱስ እና ለቡካዮ ሳካ የተለየ ፍቅር አላቸው።

ረቡዕ 4 ጁን 2025 ጥዋት 4:00:19
ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ውስጥ በሕዝብ እና በጭነት ተሽከርካሪዎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች እና እገታዎች ተበራክተዋል። ይህ ክስተት ደግሞ ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት ላይ በሚገኘው የሰሜን ሸዋ አካባቢ በተደጋጋሚ ሲከሰት ቆይቷል። በተለይ አሊ ዶሮ የሚባለው ቦታ የጥቃት እና የእገታ ማዕከል ሆኗል እየተባለ ነው። ቢቢሲ በተለይ ይህ ቦታ ለምን የመንገደኞች እና የአሽከርካሪዎች ‘የሞት ቀጣና’ ሆነ? በሚል ለወራት የዘለቀ ምርመራ አድርጓል።

ሰኞ 18 ኖቬምበር 2024 ጥዋት 3:53:07
ግንቦት 2015 ዓ.ም. የተፈጸመው የፀጋ በላቸው ጠለፋ ብዙዎችን ያስቆጣ፣ መነጋገሪያም የሆነ የወንጀል ድርጊት ነበር። ፀጋ፤ ከአንድ ዓመት ከመንፈቅ በፊት ተጠልፋ ያሳለፈቻቸውን ቀናት በተመለከተ ለመጀመሪያ ጊዜ ለቢቢሲ በዝርዝር ተናግራለች። ከቢቢሲ ጋር በነበራት ዘለግ ያለ ቆይታ፤ ስለተጠለፈችበት መንገድ እና ስላሳለፈቻቸው ዘጠኝ ቀናት በዝርዝር ተርካለች። ከጠለፋው ነጻ የወጣችበት መንገድም አስቀድሞ በክልሉ መንግሥት ከተገለጸው የተለየ እንደሆነ ለመጀመሪያ ጊዜ ተናግራለች። ለምን ከኢትዮጵያ እንደተሰደደች እና ስለ ቀጣይ ዕቅዶቿም እንዲሁ አጋርታለች።

ሰኞ 12 ሜይ 2025 ጥዋት 4:02:02
ባለፉት ዓመታት በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች ውስጥ የሚካሄዱ ግጭቶች እና በታጣቂዎች የሚፈጸሙ እገታዎች ዜጎች በፈለጉት ጊዜ እና መንገድ በአገሪቱ ውስጥ እንዳይንቀሳቀሱ ብርቱ ስጋት ፈጥሮባቸዋል። በተለይ ደግሞ የመንገደኞች ማጓጓዣ ተሽከርካሪዎችን በማድረግ የሚፈጸሙት ያላባሩ እገታዎች በዋነኞቹ የአገሪቱ ክልሎች ውስጥ እንቅስቃሴን አዳጋች አድርገውታል። በዚህም ሳቢያ አቅሙ ያላቸው እና የግድ የሆነባቸው ሰዎች ፊታዎችን ወደ አየር ትራንስፖርት አዙረዋል።

ረቡዕ 2 ኤፕሪል 2025 ጥዋት 4:04:10
ዛሬ፣መጋቢት 24 የኦቲዝም ግንዛቤ ማስጨበጫ ቀን ነው። ይህ ዕለት በዓለም ደረጃ ታስቦ እንዲውል ለተባበሩት መንግሥታት ሐሳብ ያቀረበችው ኳታር ናት። ወደዚያው ብናቀና ዶክተር ወንድወሰን ግርማን እናገኛለን። ኦቲስቶች መኪና እንዲያሽከረክሩ የሚያስችል ከፍተኛ ምርምር ያደረጉ ኢትዮጵያዊ ናቸው።

ዓርብ 28 ማርች 2025 ጥዋት 4:04:02
የዓለም ጤና ድርጅት የኢትዮጵያ የአየር ብክለት ልኬት ከፍተኛ መሆኑን ያሳያል። ድርጅቱ እንደሚለው 99 በመቶው የዓለም ሕዝብ የሚተነፍሰው አየር ተበክሏል። ተላላፊ ላልሆኑ በሽታዎች የሚዳርገው የአየር ብክለት በኢትዮጵያ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ቢቢሲ ያነጋገራቸው ባለሙያ ይናገራሉ። ለመሆኑ በኢትዮጵያ ዋነኛ አየር በካዮች የትኞቹ ናቸው? መፍትሔውስ ምንድን ነው?

ዓርብ 7 ማርች 2025 ጥዋት 3:50:04
ፓላንዳዊቷ ዶ/ር ኤቫን የአማርኛ ቋንቋን ከ40 ዓመት በፊት ተምራ በዲግሪ ከተመረቀች በኋላ ከሃያ ዓመታት በላይ በማስተማር በርካቶችን በአማርኛ ቋንቋ ዲግሪ አስይዛለች። የምታስተምርበት ዩኒቨርስቲ ወደ 80 ዓመታት ለሚጠጋ ጊዜ አማርኛን እያስተማረ ነው። አማርኛ ቋንቋን “ፏፏቴ ነው” የምትለው ዶ/ር ኤቫን በአገሯ በአማርኛ አስተርጓሚነት ትሠራለች። ለመሆኑ እንዴት ከአማርኛ ጋር ተዋወቀች?

ሐሙስ 19 ዲሴምበር 2024 ጥዋት 4:54:19
በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ጉልህ ስፍራ ካላቸው ፖለቲከኞች መካከል ጃዋር መሃመድ አንዱ ነው። ለዓመታት ያህል በኦሮሚያ የነበሩ ትግሎችን እንዲሁም ተቃውሞዎችን ከጀርባም ሆነ ከፊት ሆኖ በማስተባበር እና በመምራት ግንባር ቀደም ነው።የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ፓርቲ አመራሩ ጃዋር ከትውልድ አንስቶ በፖለቲካ ህይወቱ የተጓዘበትን ህይወቱ ላይ የሚያጠነጥን ‘አልጸጸትም’ የተሰኘውን መጽሐፍ ታህሳስ 10/ 2017 ዓ.ም በኬንያዋ መዲና ናይሮቢ ያስመርቃል። ጃዋር መሃመድ በአገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ፣ በቀጣይ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ስለሚኖረው ሚና፣ አገሪቱ ስላለችበት ሁኔታ ከቢቢሲ አማርኛ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ሰኞ 30 ሴፕቴምበር 2024 ጥዋት 4:13:42
ይህ ጥናታዊ ዘገባ የዩኒቨርስቲ መምህራን ላይ ያጠነጥናል፤ ከእነርሱም ውስጥ ፒኤችዲ (ዶክትሬት) የሚማሩት ላይ ያተኩራል። መምህራኑ የበለጠ በተማሩ ቁጥር የበለጠ እየተራቡ እንደሆነ ያወሳሉ። ቢቢሲ በርከት ያሉ የፒኤችዲ ተማሪዎችን ለወራት ቃለ መጠይቅ ሲያደርግ ቆይቷል። ከጉዳዩ ስፋት የተነሳ የብዙዎቹ አስቸጋሪ የኑሮ ሁኔታ እና ታሪክን በሚወክሉ በአምስት መምህራን ተወክሎ ቀርቧል።

ሰኞ 17 ማርች 2025 ጥዋት 3:41:37
“የብዙ ኢትዮጵያዊ ደም ነው የወሰደው። የኢትዮጵያ ደም ነው ያለህ እንለዋለን” ይህ በሶማሊያ የኢትዮጵያ የቀድሞ አምባሳደር ወንድሙ አሳምነው ለአሁኑ የጁባላንድ ግዛት ፕሬዚዳንት ማዶቤ በቀልድ መልኩ ጣል ያደርጉላቸው ነገር ነው። ይህ በቀልድ የተለወሰ መሪር እውነታ ነው። እውነታው የሶማሊያዋን ራስ ገዝ ጁባላንድን ላለፉት 12 ዓመታት ያስተዳደረው ማዶቤ በአንድ ወቅት በኢትዮጵያ ጦር ክፉኛ ቆስሎ በአዲስ አበባ ህክምና አድርጓል።

ቅዳሜ 19 ኤፕሪል 2025 ጥዋት 4:57:24
ወታደራዊው አስተዳደር ደርግ የአገሪቱን የመሪነት መንበር ከያዘ በኋላ የዛሬ 50 ዓመት የዕድገት በኅብረት ዘመቻን አወጀ። በዚህም ከ10ኛ ክፍል እስከ ዩኒቨርስቲ ያሉ ተማሪዎች እና መምህራን በገጠሪቱ ኢትዮጵያ ተሰማርተው በማስተማር እና በልማት ሥራዎች ላይ እንዲሳተፉ አድርጎ ነበር። በዚህ ዘመቻ የተሳተፉ የዚያ ዘመን አፍላ ወጣቶች ከአምስት አሥርታት በኋላ በጋራ ተሰባስበው ያሳለፉትን ጊዜ አስታውሰዋል። ትዝታቸውንም ለቢቢሲ አጋርተዋል. . .

ቅዳሜ 3 ሜይ 2025 ጥዋት 4:55:41
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የከበሮ፣ ጽናጽል እና መቋሚያ ንድፎችን በአዕምሯዊ ንብረትነት ማስመዝገቧን ተከትሎ ጉዳዩ ሲያከራክር ሰንብቷል። ምዝገባው ሌሎች ቤተ እምነቶች እነዚህን መገልገያዎች “እንዳይጠቀሙ የመከልከል መብት ይሰጣል ወይስ አይሰጥም?” የሚለው የክርክሩ ማጠንጠኛ ሆኗል። በዚህ ጉዳይ ላይ የቤተ ክርስቲያኗ ኃላፊዎች ያላቸው አረዳድ እና የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን አቋም የተለያየ ነው።