ረቡዕ 22 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 10:29:17
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፓትሪያርክ አቡነ ማትያስ በአገር ውስጥ የሚታዩ ግጭቶች ቆመው ለሰላም እና እርቅ ዕድል እንዲሰጥ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ የበኩሉን ጥረት እንዲያደርግ ጥሪ አቀረቡ። ሊቀ ጳጳስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ የቅዱስ ሲኖዶስ ዐቢይ ጉባኤ መጀመሩን አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕከት በአገር ውስጥ የሚታዩ የርስ በርስ ግጭቶች እንዲቆሙ እና ለሰላም እና ለእርቅ ዕድል እንዲሰጥ ጠይቀዋል።
ረቡዕ 22 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 6:05:36
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሕገ ወጥ መንገድ ገንዘብ ያስተላልፋሉ ያላቸው የሀዋላ ተቋማት፣ ገንዘብ ላኪዎች እና ተቀባዮች ላይ የተጠናከረ እርምጃ ሊወስድ መሆኑን አስጠነቀቀ። ዶ/ር እዮብ እንወስደዋለን ያሉት እርምጃ “የማያዳግም” መሆኑን ጠቁመው፤ “የኢትዮጵያን ሕግ የጠበቀ፤ የዓለም አቀፍ ሕግን የጠበቀ፤ የተናበበ እርምጃ” እንደሆነም ተናግረዋል።
ረቡዕ 22 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 7:25:09
በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ኖኖ ወረዳ ከጉራጌ ዞን የተነሱ ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት 12 ሰዎች ሲገደሉ የፀጥታ ኃይሎች ደግሞ 22 መግደላቸውን ነዋሪዎች እና የአካባቢው ባለሥልጣን ለቢቢሲ ተናገሩ። በኖኖ ወረዳ ሀሎ ዲኒቂ መንደር ባለፈው ቅዳሜ ጥቅምት 8/2018 ዓ. ም. ምሽት ላይ በተፈጸመው ጥቃት 22 ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ሲናገሩ የኖኖ ወረዳ አስተዳዳሪ ግን የተገደሉት 12 ሰዎች መሆናቸውን ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ገልጸዋል።
ማክሰኞ 21 ኦክቶበር 2025 ከሰዓት 3:48:12
በሶማሌ ክልል ሺንሌ ከተማ ውስጥ በደረሰ የባቡር አደጋ ቢያንስ 15 ሰዎች ሲሞቱ 27 ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን የአካባቢው ባለሥልጣናት ለቢቢሲ ገለጹ። ሰኞ፣ ጥቅምት 11/ 2018 ዓ.ም. ሌሊት ላይ በደረሰው በዚህ አደጋ ከሞቱት ሰዎች በተጨማሪ ሌሎች በርካታ ሰዎች ከባድ ጉዳት እንዳጋጠማቸው የክልሉ የኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ እና የሺንሌ ወረዳ አስተዳዳሪ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ማክሰኞ 21 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 5:45:52
ኢትዮጵያ ውስጥ ባሉ የፖለቲካ እንቅስቃሴዎች “መገንጠልም፣ መጠቅለልም” አይሠራም ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ተናገሩ። “ከሰሜን እስከ ደቡብ” ባለው የአገሪቱ ክፍሎች “ልገንጠል” በሚል የተደራጁ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንዳሉ የገለጹት ዐቢይ፤ “አንዱም አገሩን አያውቅም” ሲሉ ተችተዋል።
ረቡዕ 15 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 9:07:52
ኢትዮጵያ በጊዜው ያልከፈለችውን የአንድ ቢሊዮን ዶላር ዩሮ ቦንድ በተመለከተ በገንዘብ ሚኒስቴር እና በግል አበዳሪዎች ኮሚቴ መካከል ሲደርግ የነበረው ድርድር ያለ ስምምነት ተጠናቀቀ። ገንዘብ ሚኒስቴር ለቀናት በቆየው ንግግር “ጉልህ መሻሻል” መታየቱን ቢገልጽም የአበዳሪዎች ኮሚቴ ግን ድርድሩ “ፍሬ አልባ” ደረጃ ላይ በመድረሱ “ሕጋዊ አማራጭ” ሊከተል እንደሚችል አስታውቋል።
ዓርብ 17 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 7:03:01
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ከተጠናቀቀ በኋላ የግብፅ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጠንካራ ንግግር እየሰነዘሩ ነው። ፕሬዝዳንት አል ሲሲ አገራቸው የውሃ ደኅንነቷን ለማስጠበቅ አስፈላጊውን ሁሉ እርምጃ እንደምትወስድ ከተናገሩ ከቀናት በኋላ ጠቅላይ ሚኒስትራቸው ሞሰጣፋ ማደቡሉ ደግሞ ግብፅ በአባይ ውሃ ላይ ያላትን ታሪካዊ እና ሕጋዊ መብት አሳልፋ አትሰጥም ብለዋል። ይህ ተከታታይ የግብፅ ባለሥልጣናት ንግግር ምን ያመለክታል?
ሰኞ 13 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 10:20:19
ከሦስት ወራት ገደማ በፊት የከተማ ማዘጋጃ ቢሮ በታጣቂዎች በተቃጠለባት የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሏ በርበር ከተማ በተፈጸመ አዲስ ጥቃት የቀበሌ ቢሮ መቃጠሉን ነዋሪዎች እና ባለሥልጣናት ገለጹ። የአካባቢው ነዋሪዎች እና ባለሥልጣናት በከተማዋ ለተፈጸመው ጥቃት በአጎራባቹ ኦሮሚያ ክልል የሚንቀሳቀሰውን ‘የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት’ ታጣቂ ቡድንን ተጠያቂ አድርገዋል።
ማክሰኞ 14 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 3:57:07
በመካከለኛው ምሥራቅ ኃያል እና ብቸኛዋ የአይሁዶች አገር የሆነችው እስራኤል በዙሪያዋ ካሉ አገራት ሁሉ በዕድሜ ትንሿ ናት። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ማብቃት በኋላ በአውሮፓውያኑ 1948 የእስራኤል እንደ አገር መመሥረት በአካባቢው አሁን ድረስ እየተካሄደ ያለ ለውጥን አስከትሏል። ለመሆኑ በየዕለቱ የዓለም መገናኛ ብዙኃን ስሟን ሳያነሱ የማያልፏት ይህች አገር እንዴት ተመሠረተች?
ረቡዕ 8 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 4:04:56
በጉንፋን፣በኢንፍሉዌንዛ እና በኮቪድ መካከል ያሉ የህመም ምልክቶች ይመሳሰላሉ።ሆኖም በሽታዎቹን ለመለየት የሚረዱ ጥቂት ምልክቶች አሉ።
ሐሙስ 9 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 4:00:49
ከትግራይ ክልል ተወክለው የፕሪቶሪያ ስምምነት ተፈራራሚ ከነበሩት መካከል አንዱ የሆኑት አቶ አሰፋ አብርሃ በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ውጊያ ሊነሳ የሚችልበት ዕድል “ያለ አይመስለኝም” ብለዋል። አቶ አሰፋ ከቢቢሲ ትግርኛ ጋር በትግራይ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ባደረጉት ቃለ ምልልስ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ወደ ጦርነት ሊገቡ አይችሉም ያሉበትን ምክንያት ሲያስረዱ ሁለቱ መሪዎች ሳዑዲ አረቢያ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ እንዲሁም “ዓለም በሙሉ ባለበት የፈረሙት ስምምነት አላቸው” በማለት አብራርተዋል።
ረቡዕ 24 ሴፕቴምበር 2025 ጥዋት 4:03:09
የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ በአገራቸው በሰላም ማስከበር ላይ የሚሰማሩ የኢትዮጵያ እና የግብፅ ወታደሮች ወደ ግጭት ሊገቡ የሚችሉበት ምክንያት እንደሌለ በመግለጽ “የውክልና ጦርነት” አይኖርም አሉ። ፐሬዝዳንቱ ከቢቢሲ ፎከስ ኦን አፍሪካ ቴሌቪዥን ጋር በነበራቸው ቃለ ምልልስ ላይ እንደተናገሩት በሁለቱ አገራት መካከል “በሶማሊያ ምድር” የሚካሄድ ጦርነት እንደማይኖር እና ሶማሊያም ይህንን እንደማትፈቅድ አሳውቀዋል።
እሑድ 12 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 4:43:31
ገላችንን መታጠብ ያለብን ጠዋት ነው ወይስ ማታ የሚለው ጉዳይ አከራካሪ ነው። ብዙዎች ጠዋት እንቅልፍ የተጫጫነው ሰውነታቸውን ለማነቃቃት ሰውነታቸውን ይታጠባሉ። ቢያንስ ለአሥር ደቂቃ መታጠብ አካልን እንደሚያነቃቃ የሚያምኑ ጥቂት አይደሉም። ለመሆኑ በጉዳዩ ላይ ሳይንስ ምን ይላል? ለጤናስ የሚጠቅመው ጠዋት መታጠብ ነው ማታ?
እሑድ 12 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 4:44:40
በውሃ ውስጥ የሚገኘው ፍሎራይድ ጥርስን ለማጠናከር እና መቦርቦርን ለመከላከል ይረዳል።
ማክሰኞ 7 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 4:00:50
ፍፁም ያልሆነ የማስታወስ ችሎት እና የተጣረሰ ትዝት የጤናማ አእምሮ መገለጫዎች ናቸው ይላሉ ኒውሮሳይንቲስቱ ቻራን ራንጋናት በቅርቡ ባሰተሙት መፅሐፍ። እንዴት?
ሐሙስ 18 ሴፕቴምበር 2025 ጥዋት 4:07:13
የዓለማችን ኃያሏ አገር መሪ ዶናልድ ትራምፕ ለጉብኝት ወደ ዩናይትድ ኪንግደም ገብተዋል። በዚህ እና በሌሎችም ጉዟቸው ላይ የሰማይ ላይ ቤተ መንግሥት በተባለው ‘ኤር ፎርስ ዋን’ አውሮፕላን እና ‘ዘ ቢስት’ በተባለው መኪና ይንቀሳቀሳሉ። እነዚህ የፕሬዝዳንቱ ልዩ መጓጓዣዎች ከሌሎቹ በምን ይለያሉ?
ዓርብ 12 ሴፕቴምበር 2025 ጥዋት 3:55:12
ከአስር ዓመት በፊት ወደ ኖርዌይ ለትምህርት አቅንቶ በኢትዮጵያ ውስጥ በነበረው ፖለቲካዊ ሁኔታ ለመመለስ ያልቻለው አማኑዔል ራጎ በአሁኑ ወቅት በኖርዌይ ፖለቲካ ውስጥ ንቁ ተሳታፊ ነው። በትውልድ አገሩ ሳለ የዩኒቨርስቲ መምህር የነበረው አማኑዔል የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ አባል እንደነበረ ይናገራል። ዜግነት ባገኘባት ኖርዌይ የክርስቲያን ዲሞክራቲክ ፓርቲ አባል በመሆን ለምክር ቤት አባልነት ተወዳድሯል።
ዓርብ 12 ሴፕቴምበር 2025 ጥዋት 3:57:00
በየሳምንቱ በባለሙያዎች የሚመከረው ያህል የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለማድረግ ብዙዎች ይቸገራሉ። የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለልብ ጤና ጠቃሚ ነው። የደም ግፊትንን፣ በስትሮክ የመያዝ ዕድልንና የኮሌስትሮል መጠንንም ይቀንሳል።ሁሌም የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለማድረግ ተነሳሽነትና ጊዜ ላይገኝ ይችላል።አበረታች ውጤት ለማየት ምን ያህል ሰዓት እንቅስቃሴ ማድረግ ነው የሚመከረው? የሚለውን ብዙዎች ይጠይቃሉ።
ረቡዕ 15 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 6:07:29
በበይነ መረብ በተፈጸመ ማጭበርበር የተገኘ ነው የተባለ ከ14 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚያወጣ ቢትኮይን መያዙን የአሜሪካ መንግሥት አስታወቀ። ‘ፕሪንስ ግሩፕ’ የተባለ የካምቦዲያ የንግድ ተቋም መስራች የሆነው ቼን ዢ በማጭበርበር ወንጀሉ ተከሷል። የንግድ ሥራው በአሜሪካ እና ዩኬ ዕገዳ ተጥሎበታል። በለንደን ያሉ 19 ቅንጡ መኖሪያዎችም ታግደዋል። ከመኖሪያዎቹ አንደኛው 133 ሚሊዮን ዶላር ያወጣል።
ሐሙስ 4 ሴፕቴምበር 2025 ጥዋት 4:05:19
በ19ኛው ክፍለ ዘመን የሕክምና ሳይንስ ጎመራ። አንዳንድ ለሳይንስ በጎ አመለካከት ያላቸው ሰዎች የገዛ አካላቸው ለሕክምና ቢውል ቅር እንደማይላቸው በይፋ መናገር ጀመሩ። ኑዛዜያቸውም ሃብት እና ንብረቴን ብቻ ሳይሆን ሰውነቴንም ለሕክምና ምርምር ይዋልልኝ የሚል ሆነ።
ማክሰኞ 23 ሴፕቴምበር 2025 ከሰዓት 12:37:11
የ13 ዓመቱ አፍጋኒስታናዊ ታዳጊ በመንገደኞች አውሮፕላን ጎማ ሥር ተደብቆ ከአፍጋኒስታን መዲና ካቡል ተነስቶ ኒው ደልሂ ገባ። በሰሜናዊ አፍጋኒስታን በምትገኘው ኩንዱዝ ከተማ ነዋሪ የሆነው ታዳጊው ሰኞ ዕለት አውሮፕላኑ በሕንድ በደልሂ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ካረፈ በኋላ በማኮብኮቢያው ሥፍራ ሲዘዋወር መገኘቱን ባለሥልጣናት ተናግረዋል።
ዓርብ 12 ሴፕቴምበር 2025 ጥዋት 7:30:57
የእንግሊዘኛው ሲም (SIM) ተጠቃሚን ለመለየት የሚያገለግል ሞጁል ማለት ነው። ይህ በስልካችን ውስጥ የምናስገባው ካርድ ከኔትወርክ አቅራቢያችን ጋር የምንገናኝበት ዋነኛ ክፍል ነው። በዚህም የተነሳ ጥሪ ማድረግ፣ የጽሑፍ መልዕክት መለዋወጥ እንዲሁም ዳታዎቻችንን መጠቀም እንችላለን። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ኢሲም (eSIM) አማራጭ ሆኖ የመጣ ሲሆን አዳዲስ ስልኮች የተለመደውን ሲም ካርድ ወይንም ኢሲም የመጠቀም ዕድል ነበራቸው።
ሐሙስ 28 ኦገስት 2025 ጥዋት 4:17:38
ቴክኖሎጂ በእጅጉ እየረቀቀ ባለበት በዚህ ዘመን የተለያዩ ሮቦቶች ለሰው ልጆች ፈታኝ የሆኑ ተግባራትን በቀላሉ እየከወኑ ይገኛሉ። በሕክምናው ዘርፍ ደግሞ ጥቃቅን ሮቦቶች ተሠርተው በደም ሕዋሳት ውስጥ ዘልቀው በመግባት ወሳን ሕክምናን ያከናውናሉ። እነዚህ ናኖሮቦትስ ወይም ናኖቦትስ ምንድን ናቸው? ምንስ አገለግሎት ይሰጣሉ? ኢትዮጵያዊው የዘርፉ ባለሙያ በዝርዝር ያብራራሉ።
ቅዳሜ 13 ሴፕቴምበር 2025 ጥዋት 4:56:17
በኳታር ዋና ከተማ ዶሃ ውስጥ እስራኤል ጥቃት የፈጸመችው በርካታ የሐማስ ፖለቲካ ቢሮ ባለሥልጣናት በሚኖሩበት የመኖሪያ አካባቢ ላይ ነው። በዚህ ጥቃት አስከ ስምንት የሚደርሱ ፍንዳታዎችን እና ከፍተኛ ጭስ በዶሃ ሰሜናዊ ክፍል ላይ ማየታቸውን ዓይን እማኞች ተናግረዋል። ከጥቃቱ ደቂቃዎች በኋላ ደግሞ እስራኤል ለተፈጸመው ጥቃት በይፋ ኃላፊነቱን ወስዳለች።
ረቡዕ 20 ኦገስት 2025 ጥዋት 3:56:27
የጠቅላይ ሚኒስትር ዴቪድ ቤን ጉርዮን መንግሥት በዓለም ታዋቂ የሆነው ሳይንቲስት አልበርት አንስታይን ለእስራኤል ፕሬዝዳንትነት እንዲሆን ካጩት በኋላ በዩናይትድ ስቴትስ የእስራኤል አምባሳደር አባ ኢባን አንስታይንን እንዲያነጋግሩ ተደረገ።
ሰኞ 11 ኦገስት 2025 ጥዋት 4:01:11
ሁለት ዓመት ሊሞላው በተቃረበው ጦርነት በጋዛ ሰርጥ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ሲገደሉ የግዛቲቱ አብዛኛው ክፍል ፈራርሷል። እስራኤል ዘመቻዋን ስትጀምር ያስቀመጠቻቸው ታጋቾችን የማስለቀቅ እና ሐማስን የመደምሰስ ዕቅዷ ከግቡ አልደረሰም። ከወዳጆቿ ሳይቀር ተቃውሞ ቢገጥማትም አሁን ደግሞ ጋዛን ሙሉ ለሙሉ የመቆጣጠር ዕቅድ እንዳላት ይፋ አድርጋለች። በርካታ መሪዎቹ የተገደሉበት ሐማስ ከዚህ ጦርነት በኋላ ዕጣ ፈንታው ምን ሊሆን ይችላል?
ሰኞ 28 ጁላይ 2025 ጥዋት 7:47:12
ማሱድ ፔዜሽኪያን ሐምሌ 2024 የኢራን ፕሬዝዳንት ሆነው ከተሾሙ ከአንድ ቀን በኋላ በቀጥታ ወደ ፖለቲካ እሳት ውስጥ ገብተዋል። ይህም አለመረጋጋት በሌለው በኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ መሪዎች ታሪክ ውስጥ ከታዩት ጅማሪዎች መካከል እጅግ አስደንጋጩ እና በቀውስ የታጀበ ነበር።
ማክሰኞ 15 ጁላይ 2025 ጥዋት 3:46:01
ዩናይትድ ስቴትስ የመጀመሪያውን የኒውክሌር ቦምብ ካፈነዳች ከሰማንያ ዓመታት በኋላ የኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር የመካከለኛው ምሥራቅን ወደ ግጭት ቀጣና እየቀየረው ነው።በአሁኑ ጊዜ በዓለም ላይ ዘጠኝ አገራት የኒውክሌር ጦር መሳሪያ እንዳላቸው ይታወቃል። እንዴት የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ሊታጠቁ ቻሉ? ሌሎች አገራትስ መሣሪያውን ማግኘት ከፈለጉ ይህንን ማሳካት ይችላሉ?
ቅዳሜ 5 ጁላይ 2025 ጥዋት 4:41:59
ባለፉት በርካታ አስርት ዓመታት ምዕራባውያን በአሜሪካ እየተመሩ በተለያዩ አገራት በተለይም ውጥረት በማይለየው መካከለኛው ምሥራቅ ውስጥ ታልቃ ገብተዋል። በዚህም ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ እና ወታደሮቻቸውን እንዲሁም ፖለቲከኞቻቸውን በማሳተፍ እነሱ ስጋት ወይም ችግር ያሉትን “ለመፍታት” ጣልቃ ገብተዋል። ይህ ዘገባ አሜሪካ በመካከለኛው ምሥራቅ ያደረገቻቸውን አራት ጣልቃ ገብነቶችን በማንሳት ገምግሟል።
ማክሰኞ 1 ጁላይ 2025 ጥዋት 3:57:49
በአውሮፓውያኑ መጋቢት 5/1957 ዩናይትድ ስቴትስ በወቅቱ በመሐመድ ሬዛ ፓህላቪ ከምትመራው ኢራን ጋር ለሲቪል የአውቶሚክ ኢነርጂ አጠቃቀም የትብብር ስምምነት ተፈራረመች። በ’አተምስ ፎር ፒስ’ መርሃ ግብር ጥላ ስር የነበረው ይህ ስምምነት የኢራንን የኒውክሌር መርሃ ግብር ለመጀመር መሠረት ጣለ። ለዋሽንግተን፣ በዚያ የቀዝቃዛ ጦርነት ወቅት ኢራን ተጨማሪ መስህብ ነበራት።
ሐሙስ 19 ጁን 2025 ጥዋት 3:52:56
እስራኤል ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ለአርብ አጥቢያ በፈጸመችው ጥቃት ቁልፍ የሚባሉ የኢራን የጦር አዛዦች እንዲሁም የኒውክሌር ሳይንቲስቶች መገደላቸው ያሉበትን ትክክለኛ ቦታ በተመለከተ መረጃ እንዳላት የሚያሳይ ነው። ከዚህ መረጃ እና ተልዕኮ ጀርባ ደግሞ የአገሪቱ የሥለላ ተቋም ሞሳድ እንዳለ ይታመናል። ሞሳድ ባለፉት ሰባት አስርት ዓመታት ውስጥ ከኢትዮጵያ እስከ ኢራን የፈጸማቸው ዋናዎቹ ተልዕኮዎች የትኞቹ ናቸው?
ሰኞ 23 ጁን 2025 ጥዋት 3:54:51
…የኢራን ከፍተኛ ጄነራሎች እሰራኤል ጥቃት ልትሰነዝር ትችላለች የሚለው ነገር አሳስቧቸው ስብሰባ ጠሩ። ሁልጊዜም እንደሚያደርጉት ‘የእስራኤል ነገር አይታወቅም’ ብለው ከመሬት ሥር በተዘጋጀ የምድር ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ ገቡ። ሞሳድ ግን ይህን ያውቅ ነበር። ቁልፍ ስብሰባዎች እዚህ ምድር ቤት እንደሚደረጉ መረጃ ነበረው።. . .
ዓርብ 13 ጁን 2025 ጥዋት 3:51:33
ኢራን እና እስራኤል ለረጅም ጊዜ በእጅ አዙር እንጂ በቀጥታ ግጭት ውስጥ ገብተው አየውቁም። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን አንደኛው በሌላኛው ላይ የቀጥታ ጥቃት እየፈጸሙ ከጦርነት አፋፍ ላይ መድረሳቸው አሳሳቢ ሆኗል። ለመሆኑ እስራኤል እና ኢራን ጦርነት ውስጥ ቢገቡ ምን ሊከሰት ይችላል? ሁለቱ አገራትስ በወታደራዊ አቅም ምን ያህል ይመጣጠናሉ?
እሑድ 15 ጁን 2025 ጥዋት 4:51:06
ኢራን ከግብፅ ቀጥላ ለእስራኤል እውቅና በመስጠት ሁለተኛዋ እስላማዊ አገር ነበረች። ነገር ግን ከኢራን እስላማዊ አብዮት በኋላ ይህ ግንኙነት ተበላሽቶ ከአራት አስርታት በላይ በጠላትነት እየተያዩ ቆይተዋል። ለመሆኑ የሁለቱ አገራት ግንኙነት ወደ ደመኛ ጠላትነት ለምን ተሸጋገረ?
ቅዳሜ 14 ጁን 2025 ጥዋት 4:31:37
እስራኤል በፈጸመችው ጥቃት በርካታ የአገሪቱ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዦች እና የኒውክሌር ሳይንቲስቶች መገደላቸውን ኢራን አረጋግጣለች። በጥቃቱ የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ የአየር ኃይል አዛዥን ጨምሮ ቢያንስ 20 የኢራን ወታደራዊ ኃይል ከፍተኛ አዛዦች ተገድለዋል። ይህ ኢራን የምትመካበት ወታደራዊ ኃይል ማን ነው? ምንስ አቅም አለው?
ሰኞ 20 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 4:03:57
የአመጋገብ ለውጥ በማድረግ እና ከመደበኛው ሕክምና ውጪ ያሉ አማራጭ ሕክምናዎችን በመጠቀም ከካንሰር ማገገማቸውን የሚናገሩ አሉ። ለዚህም የተለያዩ ዓይነት ምግቦች፣ ቅመማ ቅመሞች እና እንቅስቃሴዎች በዓለም ዙሪያ ካንሰርን ይከላከላኑ እንዲሁም ይፈውሳሉ በሚል ጥቅም ላይ በስፋት እየዋሉ ነው። በማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይም እየተጋሩ መነጋገሪያ ከሆኑ ሰንበትበር ብለዋል። ባለሙያዎች ምን ይላሉ? እውን ለሕመሙ መፍትሄ ይሰጣሉ?
ዓርብ 10 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 3:55:08
የዚህ ዓመት የሰላም ኖቤል ሽልማት አሸናፊ ዛሬ መስከረም 30 2018 ዓ.ም. ይፋ ተደርጓል። የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኖቤል የሰላም ሸልማት እንደሚገባቸው ሲናገሩ ቢቆዩም የኖቤል ሽልማት ኮሚቴ ግን ለቬንዚዌላዊቷ የተቃውሞ ፖለቲከኛ መሪ ማሪያ ኩሪና ማቻዶ ሰጥቷል። ለመሆኑ የኖቤል ሽልማት ምንድን ነው?
ረቡዕ 8 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 4:04:56
በጉንፋን፣በኢንፍሉዌንዛ እና በኮቪድ መካከል ያሉ የህመም ምልክቶች ይመሳሰላሉ።ሆኖም በሽታዎቹን ለመለየት የሚረዱ ጥቂት ምልክቶች አሉ።
ማክሰኞ 7 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 4:00:50
ፍፁም ያልሆነ የማስታወስ ችሎት እና የተጣረሰ ትዝት የጤናማ አእምሮ መገለጫዎች ናቸው ይላሉ ኒውሮሳይንቲስቱ ቻራን ራንጋናት በቅርቡ ባሰተሙት መፅሐፍ። እንዴት?
ሰኞ 6 ኦክቶበር 2025 ጥዋት 3:55:54
ማታ ቆንጆ እንቅልፍ ለመተኛት መሠረቱ ጥሩ አዋዋል ነው። ድካም አብዝቶ የሚሰማቸው ሰዎች የተሻለ እንቅልፍ ቢተኙ ደስ ይላቸዋል። ሁሌም በተመሳሳይ ሰዓት መተኛትና ማታ ስክሪን አለማየት ይመከራሉ። ቆንጆ ቀን በማሳለፍም የተሻለ እንቅልፍ ማግኘት ይቻላል። ጥሩ እንቅልፍ ደግሞ ድካምን ያስወግዳል።
ረቡዕ 4 ጁን 2025 ጥዋት 4:00:19
ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ውስጥ በሕዝብ እና በጭነት ተሽከርካሪዎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች እና እገታዎች ተበራክተዋል። ይህ ክስተት ደግሞ ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት ላይ በሚገኘው የሰሜን ሸዋ አካባቢ በተደጋጋሚ ሲከሰት ቆይቷል። በተለይ አሊ ዶሮ የሚባለው ቦታ የጥቃት እና የእገታ ማዕከል ሆኗል እየተባለ ነው። ቢቢሲ በተለይ ይህ ቦታ ለምን የመንገደኞች እና የአሽከርካሪዎች ‘የሞት ቀጣና’ ሆነ? በሚል ለወራት የዘለቀ ምርመራ አድርጓል።
ሰኞ 12 ሜይ 2025 ጥዋት 4:02:02
ባለፉት ዓመታት በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች ውስጥ የሚካሄዱ ግጭቶች እና በታጣቂዎች የሚፈጸሙ እገታዎች ዜጎች በፈለጉት ጊዜ እና መንገድ በአገሪቱ ውስጥ እንዳይንቀሳቀሱ ብርቱ ስጋት ፈጥሮባቸዋል። በተለይ ደግሞ የመንገደኞች ማጓጓዣ ተሽከርካሪዎችን በማድረግ የሚፈጸሙት ያላባሩ እገታዎች በዋነኞቹ የአገሪቱ ክልሎች ውስጥ እንቅስቃሴን አዳጋች አድርገውታል። በዚህም ሳቢያ አቅሙ ያላቸው እና የግድ የሆነባቸው ሰዎች ፊታዎችን ወደ አየር ትራንስፖርት አዙረዋል።
ረቡዕ 2 ኤፕሪል 2025 ጥዋት 4:04:10
ዛሬ፣መጋቢት 24 የኦቲዝም ግንዛቤ ማስጨበጫ ቀን ነው። ይህ ዕለት በዓለም ደረጃ ታስቦ እንዲውል ለተባበሩት መንግሥታት ሐሳብ ያቀረበችው ኳታር ናት። ወደዚያው ብናቀና ዶክተር ወንድወሰን ግርማን እናገኛለን። ኦቲስቶች መኪና እንዲያሽከረክሩ የሚያስችል ከፍተኛ ምርምር ያደረጉ ኢትዮጵያዊ ናቸው።
ዓርብ 28 ማርች 2025 ጥዋት 4:04:02
የዓለም ጤና ድርጅት የኢትዮጵያ የአየር ብክለት ልኬት ከፍተኛ መሆኑን ያሳያል። ድርጅቱ እንደሚለው 99 በመቶው የዓለም ሕዝብ የሚተነፍሰው አየር ተበክሏል። ተላላፊ ላልሆኑ በሽታዎች የሚዳርገው የአየር ብክለት በኢትዮጵያ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ቢቢሲ ያነጋገራቸው ባለሙያ ይናገራሉ። ለመሆኑ በኢትዮጵያ ዋነኛ አየር በካዮች የትኞቹ ናቸው? መፍትሔውስ ምንድን ነው?
ዓርብ 7 ማርች 2025 ጥዋት 3:50:04
ፓላንዳዊቷ ዶ/ር ኤቫን የአማርኛ ቋንቋን ከ40 ዓመት በፊት ተምራ በዲግሪ ከተመረቀች በኋላ ከሃያ ዓመታት በላይ በማስተማር በርካቶችን በአማርኛ ቋንቋ ዲግሪ አስይዛለች። የምታስተምርበት ዩኒቨርስቲ ወደ 80 ዓመታት ለሚጠጋ ጊዜ አማርኛን እያስተማረ ነው። አማርኛ ቋንቋን “ፏፏቴ ነው” የምትለው ዶ/ር ኤቫን በአገሯ በአማርኛ አስተርጓሚነት ትሠራለች። ለመሆኑ እንዴት ከአማርኛ ጋር ተዋወቀች?
ሐሙስ 19 ዲሴምበር 2024 ጥዋት 4:54:19
በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ጉልህ ስፍራ ካላቸው ፖለቲከኞች መካከል ጃዋር መሃመድ አንዱ ነው። ለዓመታት ያህል በኦሮሚያ የነበሩ ትግሎችን እንዲሁም ተቃውሞዎችን ከጀርባም ሆነ ከፊት ሆኖ በማስተባበር እና በመምራት ግንባር ቀደም ነው።የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ፓርቲ አመራሩ ጃዋር ከትውልድ አንስቶ በፖለቲካ ህይወቱ የተጓዘበትን ህይወቱ ላይ የሚያጠነጥን ‘አልጸጸትም’ የተሰኘውን መጽሐፍ ታህሳስ 10/ 2017 ዓ.ም በኬንያዋ መዲና ናይሮቢ ያስመርቃል። ጃዋር መሃመድ በአገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ፣ በቀጣይ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ስለሚኖረው ሚና፣ አገሪቱ ስላለችበት ሁኔታ ከቢቢሲ አማርኛ ጋር ቆይታ አድርጓል።
ሰኞ 30 ሴፕቴምበር 2024 ጥዋት 4:13:42
ይህ ጥናታዊ ዘገባ የዩኒቨርስቲ መምህራን ላይ ያጠነጥናል፤ ከእነርሱም ውስጥ ፒኤችዲ (ዶክትሬት) የሚማሩት ላይ ያተኩራል። መምህራኑ የበለጠ በተማሩ ቁጥር የበለጠ እየተራቡ እንደሆነ ያወሳሉ። ቢቢሲ በርከት ያሉ የፒኤችዲ ተማሪዎችን ለወራት ቃለ መጠይቅ ሲያደርግ ቆይቷል። ከጉዳዩ ስፋት የተነሳ የብዙዎቹ አስቸጋሪ የኑሮ ሁኔታ እና ታሪክን በሚወክሉ በአምስት መምህራን ተወክሎ ቀርቧል።
ሰኞ 18 ኖቬምበር 2024 ጥዋት 3:53:07
ግንቦት 2015 ዓ.ም. የተፈጸመው የፀጋ በላቸው ጠለፋ ብዙዎችን ያስቆጣ፣ መነጋገሪያም የሆነ የወንጀል ድርጊት ነበር። ፀጋ፤ ከአንድ ዓመት ከመንፈቅ በፊት ተጠልፋ ያሳለፈቻቸውን ቀናት በተመለከተ ለመጀመሪያ ጊዜ ለቢቢሲ በዝርዝር ተናግራለች። ከቢቢሲ ጋር በነበራት ዘለግ ያለ ቆይታ፤ ስለተጠለፈችበት መንገድ እና ስላሳለፈቻቸው ዘጠኝ ቀናት በዝርዝር ተርካለች። ከጠለፋው ነጻ የወጣችበት መንገድም አስቀድሞ በክልሉ መንግሥት ከተገለጸው የተለየ እንደሆነ ለመጀመሪያ ጊዜ ተናግራለች። ለምን ከኢትዮጵያ እንደተሰደደች እና ስለ ቀጣይ ዕቅዶቿም እንዲሁ አጋርታለች።
ሰኞ 17 ማርች 2025 ጥዋት 3:41:37
“የብዙ ኢትዮጵያዊ ደም ነው የወሰደው። የኢትዮጵያ ደም ነው ያለህ እንለዋለን” ይህ በሶማሊያ የኢትዮጵያ የቀድሞ አምባሳደር ወንድሙ አሳምነው ለአሁኑ የጁባላንድ ግዛት ፕሬዚዳንት ማዶቤ በቀልድ መልኩ ጣል ያደርጉላቸው ነገር ነው። ይህ በቀልድ የተለወሰ መሪር እውነታ ነው። እውነታው የሶማሊያዋን ራስ ገዝ ጁባላንድን ላለፉት 12 ዓመታት ያስተዳደረው ማዶቤ በአንድ ወቅት በኢትዮጵያ ጦር ክፉኛ ቆስሎ በአዲስ አበባ ህክምና አድርጓል።
ቅዳሜ 19 ኤፕሪል 2025 ጥዋት 4:57:24
ወታደራዊው አስተዳደር ደርግ የአገሪቱን የመሪነት መንበር ከያዘ በኋላ የዛሬ 50 ዓመት የዕድገት በኅብረት ዘመቻን አወጀ። በዚህም ከ10ኛ ክፍል እስከ ዩኒቨርስቲ ያሉ ተማሪዎች እና መምህራን በገጠሪቱ ኢትዮጵያ ተሰማርተው በማስተማር እና በልማት ሥራዎች ላይ እንዲሳተፉ አድርጎ ነበር። በዚህ ዘመቻ የተሳተፉ የዚያ ዘመን አፍላ ወጣቶች ከአምስት አሥርታት በኋላ በጋራ ተሰባስበው ያሳለፉትን ጊዜ አስታውሰዋል። ትዝታቸውንም ለቢቢሲ አጋርተዋል. . .
ቅዳሜ 3 ሜይ 2025 ጥዋት 4:55:41
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የከበሮ፣ ጽናጽል እና መቋሚያ ንድፎችን በአዕምሯዊ ንብረትነት ማስመዝገቧን ተከትሎ ጉዳዩ ሲያከራክር ሰንብቷል። ምዝገባው ሌሎች ቤተ እምነቶች እነዚህን መገልገያዎች “እንዳይጠቀሙ የመከልከል መብት ይሰጣል ወይስ አይሰጥም?” የሚለው የክርክሩ ማጠንጠኛ ሆኗል። በዚህ ጉዳይ ላይ የቤተ ክርስቲያኗ ኃላፊዎች ያላቸው አረዳድ እና የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን አቋም የተለያየ ነው።
ዓርብ 24 ሜይ 2024 ጥዋት 4:16:17
ከእንግሊዝ ታላላቅ ቡድኖች መካከል አንዱ የሆነው የአርሰናል የልብ ደጋፊ የሆኑት ወ/ሮ እቴቱ ማሞ የ65 ዓመት እናት ናቸው። ላለፉት 20 ዓመታት አርሰናልን ያለማቋረጥ ደግፈዋል። እንደብዙዎቹ የቡድኑ ደጋፊዎች ዘንድሮ አርሰናል ዋንጫ ባለማንሳቱ ቢከፉም ድጋፋቸው ግን እንደሚቀጥል ይናገራሉ። ከሁሉም ተጫዋቾች ይልቅ እሳቸው ገብረኢየሱ ለሚሉት ለጋብሬል ጀሱስ እና ለቡካዮ ሳካ የተለየ ፍቅር አላቸው።