
ቅዳሜ 22 ኦገስት 2026 ጥዋት 10:22:16
በኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ጉባኤ ሲከራክር በቆየው የአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ የከተማዋ “የኦሮሚያ ክልል መቀመጫነት በፌደራል ሕግ መንግሥት እንዲሰፍር” የሚጠይቅ ምክረ ሃሳብ መቅረቡን ምንጮች ለቢቢሲ ተናገሩ። ከተማዋ “ከኦሮሚያ ክልል ጋር የሚኖራትን ግንኙነት” በተመለከተ ግን ኮሚሽኑ የመጨረሻውን የሚለው ምክረ ሀሳብ ለመንግሥት እንደሚያቀርብ ማስታወቁን አንድ ምንጭ ገልጸዋል።

ቅዳሜ 22 ኦገስት 2026 ጥዋት 4:59:51
ለሦስት ዓመታት በቆየው የአሜሪካ መንግሥት ጊዜያዊ የሕግ ጥበቃ አማካኝነት ከለላ አግኝተው የቆዩ ኢትዮጵያውን ስደተኞች፣ አሁን ከአገር እንዲወጡ የሚያስገድዳቸው ውሳኔ በፍርድ ቤት ተላልፎባቸዋል። እንደ ኢትዮጵያዊቷ ሩት ያሉ ጥገኝነት ጠያቂዎች በአሜሪካ ለመቆየት ብቸኛ ሕጋዊ መሠረታቸው የሆነው ጊዜያዊ ከለላ መነሳቱ ቀጣይ ዕጣ ፋንታቸውን አጣብቂኝ ውስጥ ከትቶታል።

__
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር በሚደረገው ጦርነት የፍጥጫ ማዕከል የሆነው የሆርሙዝ ወሽመጥ “የአሜሪካ ግዛት ነው” ሲሉ ተናገሩ። አርብ ዕለት በደቡብ ካሪላይና ግዛት በተካሄደ የምርጫ ቅስቀሳ ዘመቻ ላይ የተገኙት ፕሬዝዳንቱ “በአሁኑ ሰዓት የሆርሙዝ ወሽመጥን እንደ የአሜሪካ ግዛት ነው የምመለከተው። የአሜሪካ ግዛት ነው” ሲሉ ለተሰበሰበው ደጋፊ ተናግረዋል።

ዓርብ 21 ኦገስት 2026 ጥዋት 10:30:59
ወደ ማጠናቀቂያው በተቃረበው የአገራዊ ምክክር ጉባኤ ላይ የአዲስ አበባ ጉዳይ መግባባት ያልተደረሰበት እና ሂደቱን ያዘገየ አጀንዳ ሆኗል። ሐሙስ ዕለት በተካሄደው ጉባኤ ላይ አዲስ አበባን በተመለከተ ክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች ስለተነሱት ምክረ ሀሳቦች ምንጮች ለቢቢሲ ተናግረዋል። የኦሮሚያ እና አማራ ክልሎች አመራሮች መካከል በመዲናዋ ጉዳይ ልዩነት መታየቱንም ተሳታፊዎቹ ገልጸዋል።

ሐሙስ 20 ኦገስት 2026 ከሰዓት 12:16:23
በትግራይ ክልል ዋና ከተማ መቀለ ውስጥ የድሮን ጥቃት መፈጸሙን እና በሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን የክልሉ ባለሥልጣናት አስታወቁ። ጥቃቱ ስለመፈጸሙ የክልሉ ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ መግለጫ ያወጣ ሲሆን፣ የክልሉ ከፍተኛ ባለሥልጣንም ለኤኤፍፒ ዜና ወኪል አረጋግጠዋል። የክልሉ ምክትል ፕሬዝዳንት እና የህወሓት ምክትል ሊቀመንበር አቶ አማኑኤል አሰፋ ለፈረንሳይ ዜና ወኪል ኤኤፍፒ እንደተናገሩት በመቀለ ከተማ ውስጥ ዛሬ ጠዋት የድሮን ጥቃት ተፈጽሟል።

ሐሙስ 20 ኦገስት 2026 ጥዋት 10:06:03
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሁለት ዓመት ሊሞላው ወራት በቀረው የሁለተኛው የሥልጣን ዘመናቸው፣ ስደተኞች እና ጥገኝነት ጠያቂዎችን ዒላማ ያደረጉ ትዕዛዞችን አሳልፈዋል። በተለያየ መንገድ ኢትዮጵያውያን ላይ ጫና ሊያሳድሩ የሚችሉ የትራምፕ አስተዳደር አራት ውሳኔዎችን እንመልከት።

ሐሙስ 20 ኦገስት 2026 ጥዋት 4:01:34
የግብፅ መንግሥት፣ በአገሪቱ የሚገነባው ‘ኤል ዳባ’ የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ማብላያዎች (ሪአክተር) ላይ “ጉድለት” እንደተገኘ በመግለፅ ግንባታውን የሚያከናውነው የሩሲያው ኩባንያ ላይ አቅርቦታል የተባለው ወቀሳ ውዝግብ አስነስቷል። “የኒውክሌር ደኅንነት አሠራር” ላይ ጥሰት ስለመፈጸሙ የወጣውን ዘገባ ተከትሎ ምላሽ የሰጡት የግብፅ ባለሥልጣናት፣ ጉዳዩን አስተባብለዋል።

ረቡዕ 19 ኦገስት 2026 ጥዋት 5:02:56
የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር፤ የጥገኝነት መብት የሌላቸው ከ5000 በላይ ኢትዮጵያውያን ከአሜሪካ እንዳይባረሩ ያደረገውን ሕጋዊ ከለላ እንዲያቋርጥ ፍርድ ቤት ፈቀደ። የቦስተን ዲስትሪክት ፍርድ ቤት ዳኛ ብሪያን መርፊ ያስተላለፉት ይህ ውሳኔ በአሜሪካ ሕጋዊ የመኖርና የመሥራት መብት ተሰጥቷቸው የነበሩ በርካታ ሰዎችን ለስደት መባረር ስጋት የሚያጋልጥ ነው።

ሐሙስ 13 ኦገስት 2026 ጥዋት 7:53:01
አንድ ወር ባስቆጠረው አገራዊ ምክክር ስምንት አጀንዳዎች ላይ ሲመክሩ የቆዩት ከአራት ሺህ በላይ ተሳታፊዎች ወደ መቋጫው እየተቃረቡ ነው። በዚህ ሂደት የአዲስ አበባ ጉዳይ ከሌሎች አጀንዳዎች በበለጠ አነጋጋሪ እና ስምምነት ላይ ለመድረስ አዳጋች ሆኖ ታይቷል። በአዲስ አበባ የምክክር አጀንዳ ላይ የተከሰተው ምንድን ነው? ያላግባቡት ጉዳዮችስ የትኞቹ ናቸው?

እሑድ 16 ኦገስት 2026 ጥዋት 6:40:52
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን)፣ በሀገራዊ ምክክር ሂደት ላይ “ከተራ የአሠራር ግድፈት” የዘለሉ “ተደጋጋሚ እና የተደራጁ ጥፋቶች ተፈጽመዋል” ሲል ከሰሰ። “ገዢው አካል መዋቅራዊ ጥሰቶችን” እንደፈጸመ በማንሳት የከሰሰው አብን፣ በአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ “የከተማዋ ነዋሪዎች ድምፅ እና ፍላጎት በአግባቡ ሳይወከል” መታለፉን ገልጿል። በሂደቱ ላይ የተፈጸሙት “ተደጋጋሚ እና የተደራጁ ጥፋቶች” የሀገራዊ ምክክሩን “ተዓማኒነት፣ አካታችነት፣ ገለልተኝነት እና ፍትሐዊነት ጥያቄ ውስጥ የሚስገቡ” እንደሆኑም ገልጿል።

ረቡዕ 12 ኦገስት 2026 ጥዋት 6:44:29
በአማራ ክልል ከተከሰተው ቀውስ ጋር በተያያዘ በሽብር ለተከሰሱት ከሦስት መቶ በላይ ፖለቲከኞች፣ ጋዜጠኞች እና ሌሎች ግለሰቦች በይቅርታ እንዲለቀቁ ሂደት ላይ ይገኛሉ። ለሽብር ተከሳሾች የቀረበው የይቅርታ ሰነድ በክልሉ ለተፈፀሙ ግድያዎች እና ጉዳቶች ተከሳሾቹ ኃላፊነት እንዲወስዱ የሚጠይቅ መሆኑን ቢቢሲ የተመለከተው ሰነድ ያሳያል።

ረቡዕ 12 ኦገስት 2026 ከሰዓት 3:28:51
በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ መተከል ዞን በታጣቂዎች በተፈፀመ ጥቃት በርካታ ሰዎች መገደላቸውን እና መቁሰላቸውን ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናገሩ። ጥቃቱ የተፈፀመው ማክሰኞ ነሐሴ 6/ 2018 ዓ. ም. ጠዋት 12 ሰዓት ላይ በዞኑ ዋና ከተማ ግልገል በለስ በሚገኙ ቤተ ክርስቲያናት እና መናኸሪያ ላይ መሆኑን ነዋሪዎች ተናግረዋል።

ሰኞ 3 ኦገስት 2026 ጥዋት 4:02:31
በአማራ ክልል ላለፉት ሦስት ዓመታት በፋኖ ኃይሎች እና በመንግሥት መካከል የሚካሄደው ግጭት የበርካቶችን ሕይወት ቀጥፏል፤ ከፍተኛ ሰብኣዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ውድመትም አድርሷል። ቢቢሲ አማርኛ ያነጋገራቸው የክልሉ ነዋሪዎች ከፍርድ ውጭ ግድያዎችን ጨምሮ ንጹኃን እስር እና እንግልትን እያስተናገዱ መሆኑን ይናገራሉ። የትጥቅ ግጭቶችን የሚመዘግበው አክሌድ ከጥር እስከ ሐምሌ 2018 ዓ.ም. ድረስ ባለው ጊዜውስት ብቻ ከስምንት ሚሊዮን በላይ ሰዎች ‘ለግጭት’ ተጋልጠዋል ብሏል። ቢቢሲ በግጭቱ በቀጥታ የተጎዱ ነዋሪዎችን እንዲሁም ባለሙያዎችን አነጋግሮ ቀጣዩን ዘገባ አሰናድቷል።

ሰኞ 10 ኦገስት 2026 ጥዋት 4:05:08
ከጋብቻ በፊት የሚደረገው የሽምግልና ሥነ ሥርዓት ከፍተኛ ድግስ እና ገንዘብ የሚፈስበት እየሆነ መጥቷል። ከሚዘጋጀው ድል ያለ ድግስ ባሻገር በመቶ ሺዎች ብር የሚያስወጡ ቄንጠኛ ግዙፍ የአበባ ‘እቅፎች’ ደግሞ የሽምግልናው ሥርዓት አካል ሆነዋል። በተለይ የሚቀርበው የአበባ ስጦታ መነጋገሪያ ሆኗል። የሽምግልና ሥነ ሥርዓት የሰርግን ቦታ እየተካ ነው? ግዙፉ የአበባ ስጦታስ ከየት የመጣ ልማድ ነው?

ቅዳሜ 8 ኦገስት 2026 ጥዋት 4:43:37
የሥዕል እና የቅርጻ ቅርጽ ባለሙያ የሆነው ዮናስ መኳንንት፤ ተወልዶ ያደገባትን፣ የእንጀራ ገመዱ የነበረችውን አዲስ አበባን ጥሎ ገጠር ከገባ ከጥቂት ወራት በኋላ ሁለት ዓመት ይሞላዋል። “እኔ እዚህ ከመጣሁ ትልቅ እረፍት ነው የሚሰማኝ። በጣም ሰላማዊ ቦታ ነው፤ ምንም ዓይነት የመኪና ድምጽ የለም፣ የምትሰማው የእንስሳት ድምጽ ብቻ ነው” ይላል።

ሐሙስ 6 ኦገስት 2026 ጥዋት 10:23:36
ከሦስት ዓመት በፊት በትግራይ ክልል መቀለ ከተማ በአሰቃቂ ሁኔታ በተገደለችው ዘውዱ ሃፍቱ ግድያ ተጠርጥረው የዕድሜ ልክ ጽኑ እስራት ተላልፎባቸው የነበሩት ሁለት ፍርደኞች በነጻ እንዲሰናበቱ ተወስኗል። ውሳኔው በሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ዘንድ ከፍተኛ ነቀፌታ ገጥሞታል። በማኅበራዊ ሚዲያ ላይም ቁጣቸውን ገልጸዋል።

ረቡዕ 5 ኦገስት 2026 ጥዋት 6:31:04
አሜሪካ አንድ የአፍሪካ ቀንድ አገርን በተመለከተ ከኤርትራ ጋር ድርድር እያደረገች ወይም ምሥጢራዊ ስምምነት ለመድረስ እየሞከረች ነው መባሉን የፕሬዝዳንት ትራምፕ ከፍተኛ አማካሪ ማሳድ ቡሎስ አስተባበሉ። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት የአረብ እና የአፍሪካ ጉዳዮች ከፍተኛ አማካሪ ማሳድረ ቡሎስ በኤክስ የማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ አሜሪካ ከኤርትራ ጋር በመሆን በየትኛውም የቀጣናው አገር ላይ እንደማታሴር ገልጸዋል።

ዓርብ 31 ጁላይ 2026 ጥዋት 3:45:20
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ወደ ሥልጣን ከተመለሱ እና ግዙፉን የአሜሪካ የእርዳታ ድርጅት ካፈረሱ በኋላ ለአፍሪካ አገራት የምትሰጠውን ድጋፍ አካሄድ ቀይራለች። ለዚህ ደግሞ ተቃውሞ እና ጥያቄ ያስነሳው ኢትዮጵያን ጨምሮ ከበርካታ የአፍሪካ አገራት ጋር የተፈራረመችው የጤና መረጃ ስምምነት ተጠቃሽ ነው።

ሰኞ 27 ጁላይ 2026 ጥዋት 3:56:11
በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ከመጠን ያለፈ ዝናብ እንዲሁም ዝናብ በወቅቱ አለመጣሉ ጉዳት አስከትሏል። ዘንድሮም አነስተኛ እና ከልክ ያለፈ ዝናብ ከፍተኛ ስጋት መደቀኑን የሚጠቁሙ ሪፖርቶች እየወጡ ነው። ለመሆኑ የኤል ኒኖ ስጋት ያለባቸው አካባቢዎች የትኞቹ ናቸው? ሁኔታው ምን ያህል አስጊ ነው?

ዓርብ 24 ጁላይ 2026 ጥዋት 3:54:25
ዓለማችንን በማይታመን ፍጥነት እየለወጠ ያለውን ሰው ሠራሽ አስተውሎት (ኤአይ) በአግባቡ መገንዘብ ምርጫ ሳይሆን ግዴታ እየሆነ የመጣ ይመስላል። ስለ ሰው ሠራሽ አስተውሎት የተዛቡ ምልከታዎች ምንድን ናቸው? ለወደፊቱ የኤአይ ዓለም እንዴት እራሳችንን ማዘጋጀት እንችላለን? የሚሉና ተያያዥ ጥያቄዎችን አንስተን ኢትዮጵያዊ የዘርፉ ባለሙያን አነጋግረናል።

ረቡዕ 29 ጁላይ 2026 ጥዋት 4:09:37
በተለያዩ ምክንያቶች በርካታ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት የመጥፋት አደጋ እንደተጋረጠባቸው ሲነገር ቆይቷል። ከእነዚህ መካከልም አውራሪስ አንዱ ነው ቢባልም ባለፉት አስርት ዓመታት ግን አንስሳው ስለመኖሩ በተጨባጭ የሚታወቅ ነገር እንደሌለ ባለሙያዎች ይናገራሉ። አውራሪስ ከኢትዮጵያ ጠፍቷል? የዱር እንስሳው ስለመኖሩ ወይም ስለመጥፋቱ ለምን ቁርጥ ያለ ነገር ለማወቅ ሳይቻል ቀረ?

ማክሰኞ 28 ጁላይ 2026 ጥዋት 3:59:29
በኢትዮጵያ ከግማሽ በላይ የሚሆኑ ሴቶች ባል ሚስቱን ለመደብደብ አሳማኝ ምክንያት ይኖረዋል ብለው እንደሚያምኑ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ያደረገው ጥናት አመለከተ። ሚስትን ለመምታት አሳማኝ ምክንያት እንዳለ የሚያስቡ ወንዶች ብዛት ከሴቶች ያነሰ ቢሆንም፤ ከዚህ ቀደም ከነበረው አንጻር በ11 በመቶ ጨምሮ ተገኝቷል።

ረቡዕ 29 ጁላይ 2026 ከሰዓት 4:41:51
የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከፍተኛ አማካሪ ከአንድ ሳምንት በፊት ካይሮ ውስጥ ከግብፅ፣ ከኤርትራ እና ከሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጋር ያደረጉት ውይይት ፀረ ኢትዮጵያ ይዘት እንደሌለው አመለከቱ። ማሳድ ቡሎስ ውይይቱ ከተካሄደ ከሳምንት በኋላ በኤክስ ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሑፍ ከአገራቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጋር ደያረጉት ንግግር “ተገቢ ያልሆነ ገጽታ ተሰጥቶት” ተዘግቧል ብለዋል።

ሰኞ 29 ጁን 2026 ጥዋት 3:58:53
የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ከአሜሪካ እና ከእስራኤል ጋር ባላት ግንኙነት የተነሳ የኢራን ዋነኛ ዒላማ ከሆነች በኋላ በቀጣናው አገራት ላይ ያላት መተማመን እየቀነሰች ነው። ለፖለቲካ፣ ለምጣኔ ሃብት እና ሌሎች ፍላጎቷን ለማሟላት ከቀጣናው ውጭ መመልከትን መርጣለች። ለዚህም ከሕንድ፣ ከዩክሬን፣ ከግሪክ፣ ከቆጵሮስ እና ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ትስስር እያጠናከረች ነው።

ሐሙስ 14 ሜይ 2026 ጥዋት 4:02:03
ፕሬዝዳንት ትራምፕ የኢራንን ባሕር ኃይል እንዳወደሙ ቢናገሩም፣ ኢራን ትናንሽ ፈጣን ጀልባዎችን በመጠቀም በሆርሙዝ ወሽመጥ የመርከቦችን እንቅስቃሴን መግታት ችላለች። ስለእነዚህ ውጤታማ የኢራን ፈጣን ወታደራዊ ጀልባዎች ምን እናውያለን?

ረቡዕ 8 ኤፕሪል 2026 ጥዋት 4:01:04
ኢራን በአሜሪካ እና በእስራኤል እየተፈጸመባት ባለው ጥቃት ከጠቅላይ መሪዋ ከአያቶላህ አሊ ኻሜኒ ጀምሮ በርካታ ቁልፍ ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ መሪዎቿ ተገድለውባታል። ነገር ግን አመራሯ ሳይፈረካከስ እየተተካካ ፍልሚያውን ቀጥሏል። ለመሆኑ የኢራን አመራር በዚህ ጦርነት ውስጥ ባለበት ጸንቶ እንዴት ሊቀጥል ቻለ?

ረቡዕ 11 ማርች 2026 ጥዋት 12:00:00
አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ ጥቃት መክፈታቸውን ተከትሎ በመካከለኛው ምሥራቅ ውስጥ ጦርነት እየተካሄደ ነው። ኢራን እየተፈጸመባት ላለው ጥቃት አጸፋውን በቀጣናው ባሉ የአሜሪካ ወዳጅ አገራት ላይ እየፈጸመች ነው። ለዚህ ደግሞ ኢራን ርካሽ እና ውጤታማ የሆኑትን ሻሂድ-136 የተባሉ አጥፍቶ ጠፊ ድሮኖችን በስፋት እየተጠቀመች ነው። ይህ በምሥል እና በቪዲዮ የተደገፈው ዘገባ ስለድሮኖቹ ምንነት ይተነትናል።

ማክሰኞ 24 ማርች 2026 ጥዋት 4:02:11
ኢራን በሕንድ ውቅያኖስ ዲያጎ ጋርሲያ ደሴት ላይ ወደሚገኘው የዩናይትድ ኪንግደም (ዩኬ) እና የአሜሪካ የጋራ ወታደራዊ ሰፈር ላይ የረዥም ርቀት ባለስቲክ ሚሳዔሎችን ማስወንጨፏ በመካከለኛው ምሥራቅ ያለውን ግጭት እየተባባሰ መምጣቱን ያሳያል። በእርግጥ ሚሳዔሎቹ ወደታቀደላቸው ዒላማ ሳይደርሱ ቀርተዋል። ነገር ግን የእስራኤል የመከላከያ ሠራዊት ጦርነቱ ከተጀመረ ወዲህ እንዲህ ዓይነት የረዥም ርቀት ሚሳዔሎች ጥቅም ላይ ሲውሉ ይህ የመጀመሪያው እንደሆነ ተናግሯል።

ሰኞ 16 ማርች 2026 ጥዋት 4:02:13
ወታደራዊ ጥቃት የመፈጸም ኃይልን የተመለከቱ ውይይቶች በሚነሱባቸው ወቅቶች አሜሪካ እና እስራኤል እንዴት ኢራንን እያጠቁ እንደሆነ በምሥል ጭምር ከማሳየት ወደ ኋላ አይሉም። በባለሙያ የተዘጋጁ ፎቶዎች እና ቪዲዮዎችን የሚጠቀመው የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ፤ ጥቅም ላይ እየዋሉ ያሉ የመሣሪያ፣ የጄት እና የመርከብ ዓይነቶችን የሚያሳዩ ልጥፎችን በየአጭር ሰዓት ልዩነት ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ይለጥፋል።

እሑድ 9 ኦገስት 2026 ጥዋት 4:57:37
የአዳም ረታ አዲሱ ‘መዝሙረ ሄላም’ የተሰኘው የረዥም ልብ ወለድ መጽሐፍ 1,008 ገጾች ሲኖሩት በአምስት ክፍሎች የተከፈለ ነው። ይህ የአዳም አዲስ መጽሐፍ ከዚህ ቀደም የሚጠቀማቸው እንደ ሕፅናዊነት ያሉ ሥነ ጽሑፋዊ ቴክኒኮችን የያዘ መሆኑን በመጽሐፉ አርትኦት ላይ የተሳተፈው ቢኒያም አቡራ ለቢቢሲ ተናግሯል። የመጽሐፉ መቼት ከዚህ ቀደም እንደነበሩ የደራሲው ሥራዎች ከ1950ዎቹ ማለቂያ እስከ 70ዎቹ መጨረሻ ያሉ ናቸው። መጽሐፉ መጠሪያ የሆነችው ሄላም ከዋና ገጸባሕሪያቱ አንዷ ስትሆን በሁሉም ክፍል ውስጥ ትገኛለች። ለሕፅናዊነት አጻጻፉ ኹነኛ ማስተሳሰሪያ በመሆን ታገለግላለች። ቢቢሲ ከአርታኢው ቢኒያም ጋር ያደረገውን ቆይታ እነሆ. . .

ቅዳሜ 1 ኦገስት 2026 ጥዋት 4:56:42
ዲጄ ሲባል መጀመሪያ የሚመጣልን ምሥል ምናልባትም የዳንስ ወለል ላይ ወዝ ወዝ የሚሉ ሰዎች እና ብልጭ ድርግም የሚል መብራት ይሆናል። እነዚህ ዲጄዎች ግን ማንኛውንም ቦታ ለሙዚቃቸው መዳረሻ ማድረግ የሚችሉ ናቸው። ጋራዥ፣ ቴአትር ቤት፣ ፀጉር ቤት፣ መጻሕፍት መደብር፣ ልብስ ሰፊ ቤት፣ ግንባታው ያልተጠናቀቀ 40/60፣ ሸክላ ሠሪ ቤት፣ ወፍጮ ቤት፣ ውይይት ታክሲ. . . የማይገቡበት የለም።

ረቡዕ 3 ጁን 2026 ጥዋት 4:03:48
የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪን ጆንግ ኡን በምሥጢር ከያዟቸው ነገሮች አንዱ የእናታቸው ጉዳይ ነው። ለ15 ዓመታት በሥልጣን ሲቆዩ አንድም ቀን የእናታቸውን ስም በአደባባይ አንስተው አያውቁም። ይህ ለምን ሆነ?